
የካቲት 05/2017(ኢዜአ)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን 75 ሺህ 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለወረዳ ማዕከላት መድረሱን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በዞኑ የሕብረት ሥራ ማህበራት ጽህፈት ቤት የምርት ግብዓት አቅርቦት ቡድን መሪ አቶ ተስፋዬ ታሲሳ እንዳሉት በምርት ዘመኑ 251 ሺህ 340 ኩንታል አፈር ማዳበሪያ ለዞኑ አርሶአደሮች ይቀርባል።
ዘንድሮ የሚቀርበው የአፈር ማዳበሪያው ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 50 ሺህ ኩንታል ብልጫ እንዳለው ገልጸው፤ በእስከሁኑ ሂደትም 75 ሺህ 400 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በዞኑ በሚገኙ የወረዳ ማዕከላት መግባቱን አመልክተዋል፡፡

በቀሩት ጊዜያት የአፈር ማዳበሪያውን በማጓጓዝ በወቅቱ ለአርሶ አደሩ ለማድረስ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
የግብዓት አቅርቦትና ስርጭቱም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ታግዞ የሚካሄድ በመሆኑ በፊት የነበሩትን አሰራር ችግሮች ከመቅረፍ ባለፈ አርሶ አደሩ ለእርሻ ልማት ስራው ማዳበሪያ በወቅቱ እንዲያገኝ እንደሚያስችል አስታውቀዋል፡፡
የዞኑ አርሶ አደሮች በአቅራቢያቸው በሚገኘው የማዳበሪያ ማሰራጫ ማዕከላት ተገኝተው በጊዜ መውሰድ እንዳለባቸውም መልዕክት አስተላልፈዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026