
አዲስ አበባ፤ የካቲት 05/2017(ኢዜአ)፦ አፍሪካ ችግሮችን በመቋቋም ዕድገቷን እንድታፋጥን ዘላቂ የፋይናንስ ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ።
46ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብስባ "የማካካሻ ፍትሕ ለአፍሪካውያንና ዘርዓ-አፍሪካውያን” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በስብሰባው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የአፍሪካ የወደፊት እጣ ፋንታ በጋራ ፈቃደኝነት እና ተግባር ላይ የተመሰረተ ነው ብለዋል።
መጪውን ጊዜ በስኬት ለመወጣት ትብብር ወሳኝ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ አፍሪካ ችግሮችን በመቋቋም ዕድገቷን ማፋጠን እንድትችልም ዘላቂ የፋይናንስ ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የአፍሪካ ሕብረት 2063 አጀንዳን ለማሳካት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን በእጥፍ ማሳደግ እንደሚያስፈልግም እንዲሁ።
የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤቱ ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው ስብሰባው ለመሪዎች ጉባኤ የሚቀርቡ አጀንዳዎችና ሌሎች ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026