የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርግ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ</p>

Feb 12, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርግ መሆኑን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።

በጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የማስጀመሪያ መርሃ ግብር የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።

ርዕሰ መስተዳድሯ በልማቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ እንዳሉት የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው።


በተለይም የከተሞችን ገፅታ ከመቀየርና ለኑሮ ተስማሚ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል።

የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት የዲዛይንና የጥናት ስራው ባለፉት ሶስት ወራት ሲከናወን መቆየቱን ጠቅሰው፤ ዛሬ ወደ ትግበራ ምዕራፍ መሸጋገሩን ገልፀዋል።

በጋምቤላ ከተማ ለተጀመረው የኮሪደር ልማት ስኬታማነት የህዝቡ ሁለንተናዊ ድጋፍና ቀና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሯ አስገንዝበዋል።


የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ሳይመን ሙን(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ርዕሰ በከተማ ጋምቤላ የሚከናወነው የኮርደር ልማት የከተማውን ማስተር ፕላን መሠረት አድርጎ የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ መዝናኛ ቦታዎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በማቀናጀት የሚተበገር ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል።

የጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ከ14 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው አራት ዋና ዋና መንገዶችን ለማልማትና ለማስዋብ ግብ ተጥሎ ወደ ስራ መገባቱን ገልፀዋል።

በዚህም መሠረት ከአቦቦ ኬላ እስከ ባሮ ድልድይ፣ ከስላሴ እስከ ዶቦስኮ፣ ከአደባባይ እስከ ዲፖ እና ከአደባባይ ቄራ መስመር በመጀመሪያው ምዕራፍ የሚሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህም በመጀመሪያው ምዕራፍ የሚከናወነው የኮሪደር ልማት ከ1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እንደሚተገበር አብራርተዋል።

የኮሪደር ልማቱ ሲጠናቀቅ የጋምቤላ ከተማን ይበልጥ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ከማድረግ ባለፉ ለኑሮ ምቹና ተስማሚ አካባቢን ለመፍጠር ያስችላል ሲሉም ከንቲባው አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026