
ጋምቤላ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርግ መሆኑን የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።
በጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት የማስጀመሪያ መርሃ ግብር የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።
ርዕሰ መስተዳድሯ በልማቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ እንዳሉት የኮሪደር ልማት ከተሞችን በማዘመን ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንዲሆኑ የሚያስችል ነው።

በተለይም የከተሞችን ገፅታ ከመቀየርና ለኑሮ ተስማሚ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል።
የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት የዲዛይንና የጥናት ስራው ባለፉት ሶስት ወራት ሲከናወን መቆየቱን ጠቅሰው፤ ዛሬ ወደ ትግበራ ምዕራፍ መሸጋገሩን ገልፀዋል።
በጋምቤላ ከተማ ለተጀመረው የኮሪደር ልማት ስኬታማነት የህዝቡ ሁለንተናዊ ድጋፍና ቀና ትብብር ሊጠናከር እንደሚገባም ርዕሰ መስተዳድሯ አስገንዝበዋል።

የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ሳይመን ሙን(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት በክልሉ ርዕሰ በከተማ ጋምቤላ የሚከናወነው የኮርደር ልማት የከተማውን ማስተር ፕላን መሠረት አድርጎ የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም የእግረኛና የብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ መዝናኛ ቦታዎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በማቀናጀት የሚተበገር ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል።
የጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያው ዙር የኮሪደር ልማት ከ14 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው አራት ዋና ዋና መንገዶችን ለማልማትና ለማስዋብ ግብ ተጥሎ ወደ ስራ መገባቱን ገልፀዋል።
በዚህም መሠረት ከአቦቦ ኬላ እስከ ባሮ ድልድይ፣ ከስላሴ እስከ ዶቦስኮ፣ ከአደባባይ እስከ ዲፖ እና ከአደባባይ ቄራ መስመር በመጀመሪያው ምዕራፍ የሚሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በዚህም በመጀመሪያው ምዕራፍ የሚከናወነው የኮሪደር ልማት ከ1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እንደሚተገበር አብራርተዋል።
የኮሪደር ልማቱ ሲጠናቀቅ የጋምቤላ ከተማን ይበልጥ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ ከማድረግ ባለፉ ለኑሮ ምቹና ተስማሚ አካባቢን ለመፍጠር ያስችላል ሲሉም ከንቲባው አብራርተዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026