የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በየዘርፉ የተመዘገቡ ውጤቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ- ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ ፤ ጥር 12/2017 (ኢዜአ) ፡- በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በተለያዩ ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ባለፉት ሶስት ዓመታት በክልሉ በተከናወኑ ተግባራትና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፤ ብልፅግና ፓርቲ በአንደኛ መደበኛ ጉባኤው ካስቀመጣቸው አቅጣጫዎች መካከል ሕብረብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር፣ ዘላቂና አስተማማኝ ኢኮኖሚ መገንባት ከዋና ዋናዎቹ ይገኙበታል።

አቅጣጫውን ተከትሎ በክልሉ በተከናወኑ ተግባራትም ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡

የህዝቡን የመልካም አስተዳደር፣ የልማትና የሰላም ጥያቄዎች መሠረት በማድረግ የተከናወኑ ተግባራትም የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ ነው ብለዋል፡፡

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል እራሱን ችሎ እንዲደራጅ መደረጉ መንግስት ለህዝቡ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ያለውን ፍላጎትና በሳል ውሳኔ ሰጪነት ያሳየበት መሆኑንም አንስተዋል፡፡

ባለፉት ሶስት ዓመታትም በክልሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በተደረገው ሰፊ ጥረት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርጉ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል።

በኢኮኖሚ ረገድም የክልሉ ትልቅ አቅም ለሆነው የግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት በተከናወነው የማዘመን ስራ ምርትናምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል።

በቡና፣ ሻይ እና ቅመማ ቅመም ዘርፍም ውጤት መመዝገቡን አመልክተዋል።

በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በማር፣በወተት፣በዶሮና በሌሎች ዘርፎች ተሰፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ በቀጣይ በሁሉም አካባቢዎች የማስፋት ስራ በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡

በማህበራዊ ዘርፍም በትምህርት ፣ በጤናና በበጎ አድራጎት ስራዎች ህብረተሰቡን በማስተባበር በተከናወነ ተግባር የመጣው ውጤት ለቀጣይ አቅም እንደሆነም ገልጸዋል።

የገቢ አቅምን ማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶት ሲከናወን የቆየ ተግባር መሆኑን ያነሱት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በ2014 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር የነበረውን የገቢ አቅም በተያዘው ዓመት 10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ለማሳደግ ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቀጣም በሁሉም ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶችን በማጠናከር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት እንደሚደረግ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.