የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>የኮሪደር ልማቱ የሞተር አልባ ትራንስፖርትን ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ መጠቀም አስችሎናል - የሐዋሳ ከተማ ነዋሪዎች</p>

Jan 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2017(ኢዜአ)፡- በሐዋሳ ከተማ የተሰራው የኮሪደር ልማት የሞተር አልባ ትራንስፖርትን ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ መጠቀም አስችሎናል ሲሉ የሐዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት በከተማዋ በኮሪደር ልማት የተገነባው መሰረተ ልማት ሞተር አልባ ትራንስፖርት ዳግም እንዲያንሰራራ አድርጓል።


ሻምበል መሰለ ስንታየሁ አስተያየት ከሰጡ ነዋሪዎች መካከል ሲሆኑ የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ መቀየሩን ጠቅሰው፥ ለብስክሌት ተለይቶ የተሰራው መንገድም ያለምንም ስጋት ለማሽከርከር እንዳስቻላቸው አንስተዋል።

ይሁን እንጂ የብስክሌት መንገድ አጠቃቀም ላይ ክፍተት መኖሩን አልፎ አልፎ እግረኞች ወደ መንገዱ እንደሚገቡ በማሳያነት ገልጸው፥ ችግሩን ለመቅረፍ ግንዛቤ መፍጠር ይገባል ብለዋል።


ሌላኛው የከተማዋ ነዋሪ አማኑኤል ፈረደ ከዚህ ቀደም ብስክሌት ሲያሽከረክር የሚጠቀመው ከሌሎች ተሽከሪካሪዎች ጋር በአንድ መስመር ላይ መሆኑን አውስቶ፤ ይህም ለአደጋ አጋላጭ ነበር ሲል ገልጿል።

የብስክሌት መንገድ ለብቻ በመሰራቱ ደህንነቱ የተጠበቀና ምቹ ሁኔታ እንደፈጠለት ተናግሯል።


አቶ ወንድወሰን ታደሰ በበኩላቸው፥ የብስክሌት መንገዱ ለሐዋሳ ድምቀትን የፈጠረ መሆኑን ጠቅሰው፥ በሌሎች የከተማዋ አካባቢዎች መስፋፋት እንዳለበት አመላክቷል።


በሐዋሳ ከተማ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሃላፊ አቶ መብራቱ ገብሬ እንደተናገሩት፥ የኮሪደር ልማት ስራው በከተማዋ የብስክሌት ተጠቃሚዎች ቁጥር እንዲጨምር አድርጓል።

በብስክሌት የሚደረግ ጉዞ ጭስ አልባ በመሆኑ የአየር ብክለትን ለመቀነስ እንዲሁም የማህበረሰቡን ጤና በመጠበቅ ረገድ የጎላ አስተዋፅኦ አለው ብለዋል።

መንግስትም ይህን ከግንዛቤ በማስገባት በኮሪደር ልማት ሥራዎች ለብስክሌት መንገድ ትኩረት ሰጥቷል ነው ያሉት።

የኮሪደር ልማቱ ምቹ የትራንስፖርት መሰረተ ልማትን ለማስፋፋት ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.