የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ከተሞችን በማዘመን የእድገት ምንጭ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ ናቸው

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የሚገኙ ከተሞችን በማዘመን ለእድገት መሰረት እንዲሆኑ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር ) ገለጹ፡፡

የክልሉና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በደብረ ብርሃን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር ) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ መንግስት ከተሞችን በማዘመን ለኢንቨስትመንት ፣ ለቱሪዝምና ለኑሮ ምቹ እንዲሆኑ ያከናወናቸው ተግባራት ውጤት እየተመዘገበባቸው ነው።


በከተሞች ተገንብተው የተጠናቀቁና በመገንባት ላይ ያሉ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ለምጣኔ ሃብት እድገት መሰረት እየጣሉ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

በደብረ ብርሃን ከተማ በመገንባት ላይ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የአስፋልት መንገድ፣ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ግንባታና ሌሎች የመሰረተ ልማት ስራዎች ለዚህ ማሳያ ናቸው ብለዋል።


የደብረ ብርሃን ከተማን ለኢንዱስትሪ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ተመራጭ እንድትሆን ለማድረግም የመሰረተ ልማት ግንባታ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፤ ከተማዋ ለአምራች ኢንዱስትሪ ያላትን ተመራጭነት በመጠቀም የማምረት አቅምን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።


በዛሬው እለት የተጎበኙትም የሶስት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት፣ ከሁለት ነጥብ ሰባት ኪሎ ሜትር በላይ የአስፋልት መንገድን ጨምሮ የሶስት ኪሎ ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገዶች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በተጨማሪም 56 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ተገንብቶ ለአገልግሎት መብቃቱን ጠቁመው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ግንባታን በማጠናቀቅ የኔትወርክ ዝርጋታ እየተከናወነ እንደሚገኝም አስረድተዋል።

የልማት ፕሮጀክቶቹም በከተማ አስተዳደሩና በነዋሪዎች የጋራ ትብብር እየተገነቡ የሚገኙ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026