የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያን ገጽታ በራስ ስታቲስቲክስና እይታ መግለጽ የመረጃ ሉዓላዊነት ማረጋገጫ ነው

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12 /2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ትክክለኛ ገጽታ በራስ ስታቲስቲክስና እይታ መግለጽ መቻሉ የመረጃ ሉዓላዊነትን የማረጋገጫ ዋነኛ መንገድ መሆኑን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) ገለጹ።

''የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነፃነት'' በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀው ሀገራዊ ጉባኤ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተካሂዷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጉባኤውን በይፋ በከፈቱበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ መረጃ የዚህ ዘመን ስትራቴጂካዊ ሀብት እና ጠንካራ ሀገረ መንግሥት የሚገነባበት ቁልፍ የሉዓላዊነት ምሰሶ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የተዋሰ አሊያም በውጭ አካላት ላይ ጥገኛ የሆነ መረጃ ሀገራዊ መሻታችንን ማሳካት ስለማያስችል፤ የፖሊሲ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የራስን መረጃ በራስ አቅም መሰብሰብ እና መተንተን ወሳኝ ግብዓት ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በከር ሻሌ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፣ ተቋማቸው የሀገሪቱን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እውነታዎችን በትክክል የሚያንጸባርቁ ስታቲስቲካዊ መረጃዎችን በስፋት በማመንጨት ላይ ይገኛል።

ተቋሙ በዋናነት ለውሳኔ ሰጪዎች፣ለእቅድና ለልማት ስትራቴጂዎች መንደፊያ የሚሆኑ ኦፊሴላዊ የስታቲስቲክስ መረጃዎችን በማመንጨት እንደሚታወቅም ጠቁመዋል።

በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት በገንዘብና በባለሙያ ድጋፍ ስም መረጃዎቻቸው እንዳይቀለበሱና የራሳቸውን እውነታ በሌሎች እይታ እንዳያዩ የመረጃ ሉዓላዊነትን ማስከበር ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል።

ከለውጡ ወዲህ የተመዘገቡት የኢኮኖሚ ሪፎርሞች እንዲሁም የሀገሪቱ የዲጂታላይዜሽን ፍጥነት እጅግ አስገራሚ መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ እያሳየች ያለው ሁለንተናዊ እድገት የሰው ሀብት ልማት አቅሟንና የባለሙያዎቿን ክህሎት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ እየተካሄደ ያለው የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ልማት ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጭምር መጥተው የሚማሩበትና የሚደመሙበት ደረጃ ላይ ደርሷል ነው ያሉት።

ይህንን የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት በመጠቀም የሀገሪቱን ትክክለኛ ገጽታ በራስ ስታቲስቲክስና እይታ መግለጽ መቻሉ የመረጃ ሉዓላዊነት ማረጋገጫ መሆኑንም አስገንዝበዋል።

ተቋሙ ለውሳኔ ሰጪነትና ለትንበያ ስራዎች የሚጠቅመውን የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስና የሮቦቲክስ እድገትን በማጣጣም የዚህ ዲጂታል ለውጥ ተጠቃሚ መሆን መቻሉ ገልጸዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ትልቅ አቅም ያለው የሰርቨር መሠረተ ልማት መገንባት መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡

የቴክኖሎጂ ስጋቶችን ለመቀነስና መረጃዎችን በአንድ ቋት ብቻ ከመያዝ ለመውጣት በቴሌ ክላውድና በተለያዩ አማራጮች መረጃዎችን የማባዛት ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እነዚህ የክላውድ አማራጮች መረጃዎችን በተለያዩ አስተማማኝ ስፍራዎች አስቀምጦ ከመጠበቅ ባሻገር፣ ለአጠቃቀማቸው ጥብቅ የሆነ የደህንነት ጥበቃ እንደሚደረግላቸውም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026