🔇Unmute
አሶሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የግብርናውን ዘርፍ በምርምር በመደገፍ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ አሰራሮች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ገለጸ።
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ባካሄደው 11ኛው ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንስ ላይ የኢትዮጵያ ግብርና ኢንስትቲዩት በምርምር የታገዙ የግብርና ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ አብራርተዋል።
ኢንስቲትዩቱ የየአካባቢውን ስነ ምህዳር የሚላመዱ እና በምርምር የተደገፉ የግብርና ውጤቶች ለአርሶአደሩ በሰርቶ ማሳያ መልክ እንዲቀርቡ በማድረግ ላይ መሆኑንም ዶክተር ፍሬው ተናግረዋል።
አርሶአደሩ የእርሻ ማሳውን በቴክኖሎጂ ታግዞ በስፋት እንዲያለማ በማድረግና የግብርናው ዘርፍ ገበያ ተኮር እንዲሆን በተከናወነው ስራም የአርሶአደሩ ህይወት እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ በሁሉም አካባቢዎች በፈጠራ የታገዙ የግብርና ፕሮጀክቶችን ለማከናወን የሚያስችል ማዕከላትን በመክፈት በተለያዩ የሰብል አይነቶችና የእንስሳት ዝርያዎች ላይ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተለይም በቅርቡ ተግባራዊ የተደረገው የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ የግብርናው ዘርፍ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ የሚያደርግ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ የምርምር ተቋማት እና የግብርናው ዘርፍ አጋር አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አስታውቀዋል።
በግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታው ተጠቃሚ ከሚሆኑት አካባቢዎች አንዱ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሆኑን የተናገሩት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ ፍኖተ ካርታው በክልሉ እየተከናወነ ያለውን የግብርና ስራ የበለጠ ውጤታማ በማድረግ የአርሶአደሩን ተጠቃሚነት እና ምርታማነት እንደሚያሳድግ አብራርተዋል።
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ የሚገኘው የምርምር ስራም ለሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተሞክሮነት የሚጠቀስ መሆኑን ዶክተር ፍሬው ጠቅሰዋል።
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026