የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የግብርናውን ዘርፍ በምርምር በማገዝ ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል አሰራር ተጠናክሮ ቀጥሏል

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የግብርናውን ዘርፍ በምርምር በመደገፍ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ አሰራሮች ተጠናክረው መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ገለጸ።

የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ባካሄደው 11ኛው ዓመታዊ የምርምር ኮንፍረንስ ላይ የኢትዮጵያ ግብርና ኢንስትቲዩት በምርምር የታገዙ የግብርና ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሁፍ አብራርተዋል።

ኢንስቲትዩቱ የየአካባቢውን ስነ ምህዳር የሚላመዱ እና በምርምር የተደገፉ የግብርና ውጤቶች ለአርሶአደሩ በሰርቶ ማሳያ መልክ እንዲቀርቡ በማድረግ ላይ መሆኑንም ዶክተር ፍሬው ተናግረዋል።

አርሶአደሩ የእርሻ ማሳውን በቴክኖሎጂ ታግዞ በስፋት እንዲያለማ በማድረግና የግብርናው ዘርፍ ገበያ ተኮር እንዲሆን በተከናወነው ስራም የአርሶአደሩ ህይወት እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጸዋል።

ኢንስቲትዩቱ በሁሉም አካባቢዎች በፈጠራ የታገዙ የግብርና ፕሮጀክቶችን ለማከናወን የሚያስችል ማዕከላትን በመክፈት በተለያዩ የሰብል አይነቶችና የእንስሳት ዝርያዎች ላይ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።

በተለይም በቅርቡ ተግባራዊ የተደረገው የግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታ የግብርናው ዘርፍ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ የሚያደርግ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ የምርምር ተቋማት እና የግብርናው ዘርፍ አጋር አካላት በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው አስታውቀዋል።

በግብርና ሽግግር ፍኖተ ካርታው ተጠቃሚ ከሚሆኑት አካባቢዎች አንዱ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሆኑን የተናገሩት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ ፍኖተ ካርታው በክልሉ እየተከናወነ ያለውን የግብርና ስራ የበለጠ ውጤታማ በማድረግ የአርሶአደሩን ተጠቃሚነት እና ምርታማነት እንደሚያሳድግ አብራርተዋል።

የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ የሚገኘው የምርምር ስራም ለሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተሞክሮነት የሚጠቀስ መሆኑን ዶክተር ፍሬው ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026