የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የምርምር ማዕከሉ የመድኃኒት ምርምርና ስርጸት ውጤታማነትን የሚያሳድግ አዲስ አቅም እየፈጠረ ነው

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦በአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት የተገነባው የምርምር ማዕከል የመድኃኒት ምርምርና ስርጸት ውጤታማነትን የሚያሳድግ አዲስ አቅም መፍጠሩን የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር መሳይ ወልደማርያም ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት በዘመናዊ መልክ የተገነባውን የምርምር ማዕከል መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።

በአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም ቅጥር ግቢ የተገነባው ዘመናዊ ተቋም ከመሠረተ ልማት ግንባታ ባለፈ፤ ራሷን የቻለችና ጤናማ የሆነች ኢትዮጵያን ዕውን ለማድረግ የሚተጋ የላቀ የዕውቀት ማዕከል ነው።

የምርምር ማዕከሉም 40 ላቦራቶሪዎችን፣ የላቁ የጂኖሚክስ እና የባዮ ኢንፎርማቲክስ፣ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራትና ብቃት የሚያረጋግጥ የባዮ ኢኩዊቫለንስ ማዕከላትን አካቷል።

የተለያዩ የመድኃኒት አምራች ኩባንያዎችም በአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት በዘመናዊ መልክ የተገነባውን የምርምር ማዕከል ጎብኝተዋል።


የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር መሳይ ወልደማርያም፤ ጉብኝቱ የሚበለፅጉ የምርምር ውጤቶች ሽግግር ውጤታማነትን ለማስጠበቅ ያለመ ነው ብለዋል።

ማዕከሉ የመድኃኒት ምርምርና ስርጸት ተወዳዳሪነትን በማሳደግ ከፍተኛ አቅም እንደሚሆን ገልጸዋል።

በማዕከሉም የመድኃኒት ምርምርና ስርጸት ሥራዎችን በላቀ መንገድ ማከናወን የሚያስችል አዲስ አቅም መፍጠር እንደተቻለ ተናግረዋል።

በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛው የመድኃኒት ተነጻጻሪነት ፍተሻ በማዕከሉ መገንባቱም ከኢትዮጵያ ባሻገር ለአፍሪካ ሀገራት ጭምር የላብራቶሪ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችል አንስተዋል።

የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት የሀገር በቀል ዕውቀቶችን መነሻ በማድረግ የተለያዩ በሽታዎችን ሕክምና መስጠት የሚያስችሉ ስምንት የምርምር ውጤቶች መበልፀጋቸውን ገልጸዋል።

በምርምር የበለፀጉ ውጤቶችም እንደ ዋና ንጥረ ነገር የሚያገለግሉና ክትባትን በተሻሻለ ቴክኖሎጂ መስጠት የሚያስችሉ መሆናቸውን አስረድተዋል።


የኢትዮጵያ መድኃኒት አምራቾች ማኅበር ፕሬዝዳንት ዶክተር ታደሰ ተፈሪ፤ በኢትዮጵያ በፖሊሲ ማዕቀፍና በተለያዩ የማሻሻያ እርምጃዎች የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።

የምርምር ማዕከሉም የኢትዮጵያን የጤና ዘርፍ የጥናትና ምርምር ውጤታማነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን ተናግረዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ የባህል ሕክምና አዋቂዎች ማኅበር ፕሬዝዳንት መጋቤ ጥበብ መሪጌታ መንግስቱ ደስታ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ የባህል ሕክምና ውጤታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።


ማዕከሉ በዘርፉ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎችን የሚያግዝ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የኢትዮጵያ አነስተኛ መድኃኒት አምራቾች ዘርፍ ማኅበር ፕሬዝዳንት ሀሺም አሕመድ ናቸው።


የዜኒት ገብስ እሸት ኢትዮጵያ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ሰለሞን ገብረእግዚእ በበኩላቸው፤ በማዕከሉ የተፈጠረው የምርምር ምኅዳር የመድኃኒት አምራቾችን አቅም ለማጎልበት እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026