የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በባህርዳር ከተማ ጸጋን ወደ በረከት የሚቀይሩ ግዙፍ የቱሪዝም ልማት ፕሮጀክቶች እየተገነቡ ነው 

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 26/2018(ኢዜአ)፦ በባህርዳር ከተማ የቱሪዝም ጸጋዎችን ወደ በረከት የሚቀይሩ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች እየተገነቡ እንደሚገኙ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በባህርዳር ከተማ በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገነባውን ፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና የሆቴል ፕሮጀክት ግንባታን አስጀምረዋል።


በታሪካዊው ጣና ሆቴል ባለበት ሥፍራ ላይ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት የሚገነባው ይህ ዓለም አቀፍ ሆቴል በ18 ወራት ውስጥ ተገንብቶ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ​ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ለባህርዳር ከተማና ለሀገራችን የቱሪዝም መዳረሻነት ከፍታና ለኢኮኖሚ መነቃቃት ትልቅ ብስራት ነው ብለዋል።

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በእርሻ፣ በማዕድንና በሌሎች ዘርፎች የሚያስመዘግበው አስደናቂ ስኬት የግሉ ዘርፍ በኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተውን ከፍተኛ ሚና በተግባር የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም የኢንቨስትመንት ግሩፑ በፈታኝ ወቅት ቀድሞ በመገኘትና ክፍተቶችን በመሙላት በኩል የላቀ ተምሳሌትነት መገለጫ እንደሆነም ተናግረዋል።

በባህርዳር ግንባታው የተጀመረው ሆቴል ሲጠናቀቅም ጸጋን ወደበረከት በመቀየር ኢትዮጵያ ዘመኑን የዋጀና ዘላቂ ኢኮኖሚ ለመገንባት በጀመረችው ጉዞ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን አንስተዋል።


በተለይም በአካባቢው ካሉ የተፈጥሮና ሠው ሠራሽ የቱሪዝም ፀጋዎች ጋር ተዳምሮ ለባህርዳርና ለአካባቢው ዕድገት ትልቅ ዕድል ይዞ እንደሚመጣም አስረድተዋል።

መንግሥት የኢትዮጵያና ከተሞቿን የቱሪዝም መዳረሻነት ከፍ የሚያደርጉ ትውልድ ተሻጋሪ ፕሮጀክቶች እንዲሳኩ ለማድረግ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

የፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና ሆቴል ፕሮጀክት በፍጥነት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ለማብቃት መትጋት እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጀማል አህመድ በበኩላቸው፥ ኩባንያው መንግሥት የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ለቱሪዝም ዘርፉ መነቃቃት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው ብለዋል።


በባህርዳር የሚገነባውን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል በ18 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

ሚድሮክ በተለያዩ ከተሞች ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ዕድገት ገንቢ ሚና የሚወጡ ዘመናዊ ሆቴሎችን እየገነባ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

በ3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጪ የሚገነባው የፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና ሆቴል ​በ32 ሺህ 440 ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፍ ሲሆን ​120 ዘመናዊ መኝታ ክፍሎችና አራት ዓለም አቀፍ ሬስቶራንቶች፣ ​ከ1 ሺህ በላይ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ትልቅ አዳራሽና የመዋኛ ገንዳን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶችን አካቷል።​

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026