🔇Unmute
ድሬደዋ፤ሚያዝያ 22/2018 (ኢዜአ)፡-በዐውደ ርዕዩ የቀረቡ የፈጠራ ውጤቶች ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ጥረቶች ማሳያ መሆናቸውንየድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ።
"ሳይንስና ቴክኖሎጂ፤ ለፈጣን አገራዊ ዕድገትና ለውጥ" በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀውና በድሬዳዋ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተሰሩ የቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ውጤቶች ዐውደ ርዕይ በድሬዳዋ ተጀምሯል።

ዐውደ ርዕዩን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ የአስተዳደሩ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አብዲ ሙክታር፣ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ እና ሌሎች አመራሮች ከፍተውታል።
ከንቲባ ከድር በወቅቱ እንዳሉት፤ በዐውደ ርዕዩ የቀረቡ የፈጠራ ውጤቶች ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተጀመሩ ዘርፈ ብዙ ጥረቶች ማሳያ ናቸው።

በመጀመሪያና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እየተከናወኑ የሚገኙት የሳይንስና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገርም አስተዳደሩ ድጋፉን እንደሚያጠናክር ተናግረዋል።
በዐውደ ርዕዩ የቀረቡት የፈጠራና የቴክኖሎጂ ውጤቶች የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ በመሆናቸው ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር በማስተሳሰር ፈጠራዎቹን ወደ ጥቅም የማሸጋገር ስራ በትኩረት ይከናወናል ብለዋል።
የብልፅግና ጉዞው በፍጥነትና በጥራት የሚሳካው ለቴክኖሎጂ ውጤቶች ልዩ ትኩረት እና ድጋፍ በማድረግ መሆኑንም አንስተዋል።
የአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ በበኩላቸው፤ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በድሬዳዋ በሚገኙ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለቴክኖሎጂ እና ለሳይንስ ፈጠራዎች ልዩ ትኩረት መሰጠቱን አስረድተዋል።

የአሁኑ የትምህርት ቤቶች የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችም የአሰራርና አደረጃጀቶች እንዲሁም የድጋፍ እና ክትትል ውጤቶች ናቸው ብለዋል።
በትምህርት ቤቶቹ የተሰሩት የቴክኖሎጂ ውጤቶች የተማሪዎችን የፈጠራ አቅም የሚያሳዩ በመሆናቸው ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።
የፈጠራ ስራዎቹም የበለጠ ዳብረው ለአምራች ኢንተርፕራይዞች፣ ለኢንዱስትሪዎች እና ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጥቅም እንዲውሉ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ዛሬ በተከፈተው እና ለሶስት ቀናት በሚቆየው ዐውደ ርዕይ ላይ በመስኖ፣ በኤሌክትሪክ፣ በአገልግሎት፣ በህክምና፣ በመማር ማስተማርና ለሌሎች ዘርፎችም የሚያግዙ የፈጠራ ስራዎች ቀርበዋል።
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026