የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የልማት ስኬቶች የሚያደርገውን ድጋፍ ይበልጥ እንደሚያሳድግ አስታወቀ

Apr 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፦የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ የተመዘገቡ የሪፎርም እና የልማት ስኬቶችን ለማስቀጠል የሚያደርገውን ድጋፍ ይበልጥ እንደሚያሳድግ አስታወቀ።

የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክ ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ በዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ነው።

በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ ከስብሰባው ጎን ለጎን፣ከዓለም ባንክ የኦፕሬሽን ማኔጂንግ ዳይሬክተር አና ቤርዴ ጋር ውይይት አድርጓል።


ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሪፎርም ሂደትና እያጋጠሙ ያሉ ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖዎችን በዝርዝር ያቀረቡ ሲሆን፤የልማት ስኬቶችን ዘላቂ ለማድረግ የዓለም ባንክ ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።

ሚኒስትሩ የዓለም ባንክ የፋይናንስ አቅርቦቱን እንዲያሰፋና ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ የድጋፍ ማዕቀፍ እንዲዘረጋ ጠይቀዋል።

የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለማረጋገጥ በኢትዮጵያ መንግሥት፣በዓለም ባንክና በአይኤምኤፍ መካከል የተቀናጀ የድጋፍ ጥቅል ማሰባሰብ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር ተደርጓል።

የዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አና ቤርዴ በበኩላቸው፣የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ያለውን ጽኑ አጋርነት ያረጋገጡ ሲሆን፤ በዚህ ወሳኝ ወቅት ከልማት አጋሮች ጋር በመቀናጀት ተቋሙ ድጋፉን ይበልጥ ለማሳደግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ልዑክ በዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ የተመዘገቡ ስኬቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን፤ የዕዳ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ከግል አበዳሪዎች ጋር እየተደረገ ያለው ውይይት ውጤታማ መሆኑን ገልጿል።

በተጨማሪም ሁለቱ ወገኖች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን የኃይል ተጠቃሚ የሚያደርገውንና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሽግግር የማፋጠን አላማ ያለውን "Mission 300" የተሰኘ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት መርሃ ግብር ተፈጻሚነት ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

ሁለቱ ወገኖች ለቀውሶች ፈጣን ምላሽ የሚሰጡ ድጋፎችን ለማቀላጠፍና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨባጭ የልማት ውጤቶችን ለማምጣት በጋራ ለመሥራት ጽኑ ቁርጠኝነት መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026