🔇Unmute
ጎንደር፤መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል የነዳጅ አቅርቦት ችግርን ለመፍታትና የተቀመጠውን ስትራቴጂ ለማሳካት የተቋቋመው ግብረ ሃይል ወደ ስራ መግባቱን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡
ቢሮው ነዳጅን በቁጠባና በፍትሃዊነት ለመጠቀም እንዲቻል በተቀመጠው ስትራቴጂ ዙሪያ በጎንደር ከተማ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ዛሬ ውይይት አካሄዷል፡፡

በመድረኩ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ዋና አማካሪ መሃመድ ጀማል (ዶ/ር) እንደገለፁት አለም አቀፍ የነዳጅ ቀውሱ እያሳደረ ያለውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ለመሻገር በክልሉ በየደረጃው የተቋቋመው ግብረ ሃይል ወደ ስራ ገብቷል፡፡
ነዳጅን ለታለመለት ዓላማ ብቻ በማዋል በቁጠባና በፍትሃዊነት በመጠቀም ረገድ ቅድሚያ ለተሰጣቸው የትራንሰፖርት ዘርፎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል፡፡
ፍትሃዊ የነዳጅ ስርጭት ስርዓትን በማስፈን ህገ ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለመቆጠጣርና እርምጃም ለመውሰድ እንዲቻል ግብረ ሃይሉ በየደረጃው ተልኮ ተቀብሎ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በክልሉ በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘና ግምቱ ከ55 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ 300 ሺህ ሊትር ናፍጣና 155 ሺህ ሊትር ቤንዚን በውርስ ለመንግስት ገቢ እንዲሆን መደረጉን ገልጸዋል፡፡
አለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት ችግሩን ለመሻገር መንግስት ያስቀመጣቸውን የአጭርና የመካከለኛ ጊዜ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በአግባቡ በመተግበር ረገድ ህብረተሰቡ ሰፊ ትብብርና ተሳትፎ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡
ህዝቡ አጫጭር መንገዶችን በእግሩ በመጓዝ እንዲሁም የህዝብ ትራንስፖርቶችን በአማራጭነት መጠቀም ችግሩን ለመሻገር ራሱን ማዘጋጀት እንዳለበትም አመልክተዋል፡፡

የጎንደር ከተማ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሃላፊ አቶ አለልኝ አይለው በበኩላቸው የነዳጅ አቅርቦት ችግሩን ለመቋቋም በከተማ አሰተዳደሩ የተቋቋመው ግብረ ሃይል ህገ ወጥ የነዳጅ ዝውውርና ግብይትን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡
አለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት ሲስተጓጎል በሀገራችን ላይ ያሳደረውን ተጽእኖ በጋራ መሻገር ይገባል ያሉት ደግሞ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ናቸው፡፡
የከተማው የፀጥታና የፍትህ አካላት በህገ ወጥ የነዳጅ ንግድና ዝውውር ላይ የተሰማሩ ማደያዎችንና ህገ ወጥ ነጋዴዎችን ለህግ በማቅረብና አፋጣኝ የህግ እርምጃ በመውሰድ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል፡፡
በውይይት መድረኩ ላይ በነዳጅ ስርጭትና በትራንሰፖርት ዘርፉ ላይ የተሰማሩ አካላትን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና የፀጥታ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025