የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ሚኒስቴሩ በጋሞ ዞን ያስገነባውን የጸሀይ ኃይል ማመንጫ ለአገልግሎት አበቃ

Mar 31, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አርባ ምንጭ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጋሞ ዞን ጋርዳ ማርታ ወረዳ በ500 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የጸሀይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለአገልግሎት አበቃ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታው ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ(ዶ/ር) በምረቃው ላይ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ 710 ኪሎ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚችል ሲሆን፣ 6 ሺህ 500 አባወራዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል።

ፕሮጀክቱ የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንደሚያሳልጥ ጠቅሰው፤ በተለይ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር አኳያ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።

ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የተናገሩት ሚኒስትር ዴኤታው፣ የአካባቢው ማህበረሰብ ለተገነባው መሠረተ ልማት ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርግም አሳስበዋል።

ለአካባቢው ማህበረሰብ የኃይል ስርጭቱን ለማዳረስ 7 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን መካከለኛ መስመር እንዲሁም 17 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ዝቅተኛ መስመር ተዘርግቷል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በውሃ፣ በፀሐይ ብርሃን፣ በነፋስና በሌሎች የታዳሽ ኃይል ምንጮች ወደ 150 ጊጋ ዋት ማመንጨት የሚያስችል አቅም ያላት ቢሆንም፤ እስካሁን ጥቅም ላይ የዋለው 9 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ብቻ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቁመዋል።

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር)፤ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጋርዳ ማርታ ወረዳ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረገ ፕሮጀክት ገንብቶ በማስረከቡ ምስጋና አቅርበዋል።

አካባቢው ከመሠረተ ልማት ርቆ በመቆየቱ ህዝቡ የኃይል ተጠቃሚ ሳይሆን መቆየቱን አስታውሰው፤ ፕሮጀክቱ መንግስት የገባውን ቃል በተግባር ያሳየበት ነው ብለዋል።

በተለይ የጤና ተቋማት የላቦራቶሪ አገልግሎት እንዲሰጡ እንዲሁም የትምህርት ተቋማት ቴክኖሎጂን እንዲጠቀሙ በማስቻል ረገድ ፕሮጀክቱ ጉልህ ፋይዳ እንዳለውም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026