የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በመጠበቅ በውጭ ገበያ ተፈላጊነቱን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በመጠበቅ በውጭ ገበያ ተፈላጊነቱን ለማሳደግ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ገለጸ።

የእንስሳት ጤና እና ደህንነት አዋጅ የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነት የሚያረጋግጡ ደንቦችን እንዲሁም የጥራት ማስጠበቂያ ስታንዳርዶች ተዘጋጅተው እየተሰራ ይገኛል።

ከእንስሳት ጤና አጠባበቅና አያያዝ ጀምሮ የምርት ጥራትን በተለያዩ ስታንዳርዶችን በማስጠበቅ ለገበያ ማቅረብና ተፈላጊነቱን የማሳደግ ተግባር ትኩረት ተደርጎበት በተቀናጀ መልኩ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።

ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተገናኘ ኢዜአ ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን የእንስሳት ምርት ሬጉላቶሪ መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አያሌው ሹመት፤ ሀገሪቷ ካላት ሰፊ የእንስሳት ሃብት አንፃር ተጠቃሚ እንድትሆን ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም የስጋ ምርት ለውጭ ገበያ በማቅረብ ላይ ያሉ ባለሃብቶች ጋር በቅርበት በመስራት የምርት ጥራትና ደህንነትን በማስጠበቅ ተፈላጊነቱን የማሳደግ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የቁጥጥር፣ ክትትልና ድጋፍ ስራን ጨምሮ የዘርፉን ሙያተኞች አቅምና ክህሎት የማሳደግ እንዲሁም የቄራዎች የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

ከቄራዎች የሚወጣው ደረቅ ቆሻሻ ለተፈጥሮ ማዳበሪያ እየዋለ መሆኑን ጠቁመው፤ ፍሳሽ ቆሻሻም ታክሞ ለአገልግሎት እንዲውል እየተደረገ ነው ብለዋል።

ለውጭ ገበያ የሚቀርበውን የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነት ለማስጠበቅ የዘመናዊ የኳራንቲን ግንባታ በማካሄድ የተሳካ ውጤት ማምጣት መቻሉንም ገልጸዋል።

በአጠቃላይ የእንስሳት ሀብት ልማት ስትራቴጂ በመቅረጽ ምርቱን በዘመናዊ አሰራር እሴት ተጨምሮበት ለገበያ እንዲቀርብ በማድረግ የተሻለ ገቢ ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።

በዚህም መሰረት ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን ጥራትና ደህንነት ለመጠበቅ የሚደረገው ጥረት እመርታዊ ውጤት እየተመዘገበበት መሆኑን ገልጸዋል።

የእንስሳት ምርት ጥራትና ደህንነትን በመጠበቅ ለውጭ ገበያ ተፈላጊነቱን ለማሳደግ የሚደረገው የተቀናጀ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026