የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ንግድና ኢንቨስትመንት ዝግጁ የሆነች፣ የዕምቅ ዐቅሞችና ዕድሎች መሶብ ናት - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Mar 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ንግድና ኢንቨስትመንት ዝግጁ የሆነች፣ የዕምቅ ዐቅሞችና የዕድሎች መሶብ ናት ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአዲስ አበባ አራተኛውን "Invest in Ethiopia 2026" የቢዝነስ ፎረምን ዛሬ በይፋ አስጀምረዋል።

ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ንግድና ኢንቨስትመንት ዝግጁ የሆነች፣ የዕምቅ ዐቅሞችና የዕድሎች መሶብ ናት ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት።


ኢትዮጵያ የጥንታዊ ሥልጣኔ ባለቤት ብቻ አይደለችም፤ ዛሬ በፈጣን የለውጥ ጎዳና ላይ ያለች፣ ግዙፍና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ እየገነባች የምትገኝ ሰፊና አዋጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ናት ብለዋል።

የኢንቨስትመንት መሶባችን በትጉኅና ወጣት ሕዝብ ዐቅም፣ ባልተነካ የተፈጥሮ ጸጋ እና በስትራቴጂያዊ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ የታደለ መሆኑን አመልክተዋል።

በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርማችንና በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያችን ለዘመናዊና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ የማይመቹ አሠራሮችን በቆራጥነት በመቀየር እንደ ፋይናንስና ቴሌኮም ያሉ ቁልፍ ዘርፎችን ለዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት ክፍት መደረጋቸውን ነው ያወሱት።

የመሠረተ ልማት አውታር መስፋፋቱ የሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ አስተማማኝ የኃይል ምንጭ መፈጠሩ ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ያላትን ምቹ ምኅዳርና ቁርጠኝነት ለዓለም የሚያረጋግጡ ታላላቅ ማሳያዎች እንደሆኑም ተናግረዋል።

እኛ የምንፈልገው ድጋፍ ሳይሆን አጋርነትን ነው፤ ርዳታን ሳይሆን ኢንቨስትመንትን ነው ያሉት አቶ ተመስገን፤ ለባለ ሀብቶች ምቹ፣ ግልጽና ተራማጅ የሆነ የሕግ ማሕቀፍ አዘጋጅተናልም ብለዋል።

መንግስት የኢትዮጵያ ብልጽግና የሚረጋገጠው በግሉ ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ፣ በፈጠራና በርትዕ በሚመራ የኢኮኖሚ ምኅዳር መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ካፒታል፣ ለችሎታ እና ለዕድል በሯን ወለል አድርጋ መክፈቷንም አመልክተዋል።

የዛሬው መድረክም ራዕይን ከተግባር፣ ዕቅድና መሻትን ደግሞ ከኢንቨስትመንት ጋር በማገናኘት የጋራ ብልጽግናችንን የምንቀርጽበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ አሁን በፍጥነት ወደ ከፍታ እየገሠገሠች ባለችበት በዚህ ታሪካዊ የዕድገት ጉዞ፣ ለዓለም አቀፍና ለሀገር ውስጥ ባለ ሀብቶች ኢትዮጵያ ለእናንተ ዝግጁ የሆነ፣ በዕድሎችና በስኬቶች የተሞላ ታላቅ የኢንቨስትመንት መሶብ አላት፤ ኑ አብረን እንሥራ! ሲሉም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025