የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባይተዋርነት ምላሽ የሚያገኝበት ጊዜ እሩቅ አይደለም 

Mar 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሕጋዊ፣ ታሪካዊና መልክዓ-ምድራዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ባይተዋርነት ምላሽ የሚያገኝበት ጊዜ እሩቅ አይደለም ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር የህዝብን አንድነት ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት የሚጠበቅባቸውን ገንቢ ሚና እንደሚወጡም አረጋግጠዋል።

ብሔራዊ ጥቅም የሀገርን ሉዓላዊ የግዛት አንድነት፣ የኢኮኖሚ ዕድገትና የማኅበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የዜጎች ሀገራዊ ግብ ነው፡፡

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄና ሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ስኬታማነትም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር ጠንካራ ሀገረ መንግስትን የሚያጸኑ የጋራ አጀንዳዎች ናቸው።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ለኢዜአ እንዳሉት፤ የተለያየ የፖለቲካ ርዕዮተ-ዓለም ቢኖራቸውም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር ረገድ ልዩነት ሊኖር አይገባም፡፡


የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ከብሔራዊ ጥቅም ጋር የተሰናሰለ የህልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊና መልክዓ-ምድራዊ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ መርህን የተከተለና የማይቀለበስ የህዝብ አጀንዳ መሆኑን ገልጸው፤ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባይተዋርነት ምላሽ የሚያገኝበት ጊዜ እሩቅ አይደለም ብለዋል፡፡

የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ነጻነት ጣሰው፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማስከበርና የህዝብን አንድነት ማስቀጠል የፖለቲካ መታገያ ማዕከላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡


የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ምላሽ ማስገኘት የሀገር ክብርና ህልውና ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፤ ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር ለድርድር የማይቀርብ የጋራ አቋማቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ፕሬዝደንት ዘሪሁን ገብረእግዚአብሔር በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና የህዝብ አንድነት ለድርድር የማይቀርቡ ቀይ መስመሮች ናቸው ብለዋል፡፡


የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ማስመለስን ጨምሮ የሀገርን ብሔራዊ ጥቅምና የህዝብን አንድነት ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት ሁሉ የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026