🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል የልማት ሥራዎችን ለመመልከት ባህርዳር ገብተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባህርዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና ካቢኔያቸው፣ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የባህርዳር ከተማ ነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው የተፈጥሮ ገጸ በረከት፣ የሰላምና የውበት ተምሳሌት በሆነችው፣ ታሪክን ከለመለመ ተፈጥሮ ጋር አዛምዶ በያዘው ጣና ሐይቅና በግርማዊው ዓባይ ወንዝ በታጀበችው ውቧ ባሕር ዳር ከተማ ገብተናል ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና ካቢኔያቸው፣ የባህርዳር ከተማ አመራሮች ላደረጉላቸው ደማቅ አቀባበልም አመስግነዋል።

በምርቃታቸውና በጸሎታቸው ላልተለዩን የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲሁም እንግዳን በፈገግታና በፍቅር መቀበል ለጋስ ማንነቱ ለሆነው የባሕር ዳር ከተማ ሕዝብ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ ሲሉም በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባህርዳር ቆይታቸው የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ይመለከታሉ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025