የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተተገበሩ የግብርና ምርታማነት ኢንሼቲቮች አስደማሚ ውጤት እያስገኙ ነው

Mar 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ተግባራዊ የተደረጉ የግብርና ምርታማነት ኢንሼቲቮች አስደማሚ ውጤት እያስገኙ መሆናቸውን በኢትዮጵያ የአየርላንድ ኤምባሲ ምክትል የሚሲዮን መሪ ፈርጋል ራያን ገለጹ፡፡

በኢትዮጵያና አየርላንድ መካከል የተገነባውን ታሪካዊ ወዳጅነት በግብርና የትብብር መስክ የበለጠ ለማጠናከር በቁርጠኝነት እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

ፈርጋል ራያን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያና አየርላንድ በጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ትብብር ላይ የተመሰረተ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው ብለዋል።

ይህ ዘመናትን የተሻገረ ዲፕሎማሲያዊ ወዳጅነት በግብርና ምርታማነት ትብብር ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልጸዋል።

አየርላንድ በድንች ሃብት ልማት ያካበተችውን ልምድና ተሞክሮ ለኢትዮጵያ በማጋራት የዘርፉ ምርታማነት የሚሻሻልበትን ድጋፍ እያደረገች መሆኗን አንስተዋል።

በዚህም የሀገራቱ የሁለትዮሽ ትብብር የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን የሚቋቋም የምርምር ውጤቶችን በማውጣት የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት እንዲሻሻል እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃና ባለአነስተኛ የመሬት ይዞታ አርሶ አደሮችን የሰብል ምርታማነት አቅም በማጎልበት የምግብ ዋስትናን እያረጋገጠ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

በቀጣይም ሀገራቸው በግብርና ዘርፍ ያላትን ምርጥ ተሞክሮ በማጋራት የኢትጵያን የግብርና ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ለማፋጠን በቁርጠኝነት እንደምትሰራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያንና አየርላንድን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትብብር በማጠናከር የግብርና ሙያተኞችን ለማብቃት እንደሚሰራም አንስተዋል።

ከበርካታ ዓመታት በፊት አየርላንድ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በግብርና ምርታማነት ላይ የተፈጠረባት ጫና በዜጎች የምግብ ደኅንነት ላይ ተፅዕኖ አሳድሮ እንደነበር አስታውሰዋል።

በዚህም መነሻነት በግብርና ዘርፍ የተደረጉ ዘርፈ ብዙ የኢንቨስትመንት ተነሳሽነቶች ያመጡት ለውጥ የበለጸገችና እራሷን የቻለች አየርላንድን መፍጠር እንዳስቻለ አብራርተዋል።

በኢትዮጵያም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ተግባራዊ የተደረጉ የግብርና ምርታማነት ኢንሼቲቮች አስደማሚ ስኬቶችን እያስገኙ እንደሚገኝ አንስተዋል።

የመንግስትና ዜጎች የግብርና ምርታማነትን የማሳደግ ቁርጠኝነትም የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት ማረጋገጥ የሚያስችል ምቹ መደላድል መፍጠር እያስቻለ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026