የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና በመከታተል የቴክኖሎጂ አቅማቸውን ሊያሳድጉ ይገባል - የምክርቤት አባላት

Jul 31, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና በመከታተል የቴክኖሎጂ አቅማቸውን ሊያሳድጉ እንደሚገባ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አባላት ተናገሩ።

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የ5 ሚሊየን ወጣቶችን መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎት ለማዳበር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2016 ዓ.ም የተጀመረ ኢንሼቲቭ ነው።

ኢንሼቲቩ በሁሉም አካባቢዎች እየተተገበረ ሲሆን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም ከ7 ሺህ በላይ ዜጎች ስልጠናውን በበይነ መረብ እየተከታተሉ መሆኑን የክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ኤጄንሲ አስታውቋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻደሊ ሀሰን ሰሞኑን በተካሄደው የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ ላይ የኮደርስ ስልጠና የሀገሪቱን ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚያሳልጥ እና ዜጎችን በሁሉም መስክ ተወዳዳሪ የሚያደርግ በመሆኑ ወጣቶች ስልጠናውን እንዲከታተሉ የምክር ቤት አባላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መጠየቃቸው ይታወሳል።

በዚሁ ጉዳይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የምክር ቤቱ አባላት የኮደርስ ስልጠና ለሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ከሚኖረው አስተዋጾኦ ባለፈ ለግለሰብ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

ከምክር ቤቱ አባላት መካከል አቶ ኑረዲን ዘካሪያ እንደተናገሩት የኮደርስ ስልጠና እንደ ሀገር የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ውስንነቶችን የሚቀርፍ እና ዘርፈ ብዙ ጠቃሜታ ያለው ነው።

ስልጠናው ሀገሪቱ ከጊዜው ጋር እንድትራመድ የሚያስችል በመሆኑ በተለይም ወጣቶች ለመጪው የረቀቀ የቴክኖሎጂ ዘመን ራሳቸውን ዝግጁ የሚያደርጉበት መልካም አጋጣሚ በመሆኑ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ሌላዋ የምክር ቤቱ አባል የራስወርቅ መሠረት በበኩላቸው የኮደርስ ስልጠና ወጣቶችን ያማከለ ቢሆንም ለማንኛውም ዜጋ የዕለት ተዕለት የስራ እንቅስቃሴ ጠቃሚ የሆነ መርሃግብር መሆኑን ተናግረዋል።


እንደ ምክር ቤት አባሏ ወጣቶች የመርሃግብሩ ተሳታፊ እንዲሆኑ የተለያዩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውንም አመላክተዋል።

በራሳቸውም ስልጠናውን ማጠናቀቃቸውን የገለጹት የምክርቤት አባሏ፤ ከስልጠናው የዲጅታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ዘዴዎችን እና በመደበኛ ስራቸው ላይ አጋዥ የሚሆን ዕውቀት ማግኘታቸውን አክለዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ኤጄንሲ ዳይሬክተር አቶ ይታያል በላይ እንዳሉት እስከአሁን ድረስም 7ዐዐ የሚሆኑ ዜጎች ስልጠናውን አጠናቀው የምስክር ወረቀት አግኝተዋል።


በተያዘው በጀት ዓመት ተግባሩንም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

ከበጎ ፍቃድ አገልግሎት ጋር በማስተሳሰር ወጣቱ በክረምት ወቅት ስልጠናውን እንዲከታተል ከተለያዩ ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ጋር እየሰራን እንገኛለን ብለዋል ።

ወጣቶች ሀገሪቱ ለያዘችው የዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታ መሠረት የሚሆን የኮደርስ ስልጠና እንዲወስዱ አቶ ይታያል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በክልሉ መርሃግብሩ ከተጀመረ ወዲህ ከ7 ሺህ በላይ ዜጎች በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ በዳታ ሳይንስና አርተፊሻል ኢንተለጀንስ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት ስልጠናውን እየወሰዱ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025