አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦በሳይንስ ሙዚየሙ ኢትዮጵያ አስደናቂ የሳይንስና የፈጠራ ጉዞ ላይ መሆኗን ተመልክቻለሁ ሲሉ የኩባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆርጌ ሉዊስ ገለጹ።
የኩባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆርጌ ሉዊስ ታፒያ ፎንሴካ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር በመሆን ሳይንስ ሙዚየምን ጎብኝተዋል።
በሙዚየሙ ቋሚ ኤግዚቢሽኑ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል፣ የግብርና፣ የውሃና ኢነርጂ እንዲሁም የኤሮስፔስ እና አቪየሽን ማሳያዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆርጌ ሉዊስ በሳይንስ ሙዚየም ኢትዮጵያ አስደናቂ የሳይንስና የፈጠራ ጉዞ ላይ መሆኗን ተመልክቻለሁ ብለዋል።
አፍሪካ የኋላቀርነት መጥፎ ትርክትን ዘመኑን በዋጀ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ተጨባጭ ሥራዎች እየቀየረች እንደምትገኝ ኢትዮጵያ ሁነኛ ማሳያ ናት ብለዋል።
ሳይንስ ሙዚየም ከኢትዮጵያ አልፎ አፍሪካ አሁን የደረሰችበትንና የመጪውን ዘመን የቴክኖሎጂ ዘመን ራዕይዋን የሚያሳይ መሆኑን መገንዘባቸውንም ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ እና ኩባ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ ጉዳዮች ዙሪያ ትብብራቸውን ለማጠናከር በጋራ ለመስራት መስማማታቸው ተገልጿል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025