ባህር ዳር፤ ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለውጭ ገበያ ለሚቀርቡ የሰሊጥና አኩሪ አተር ልማት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ የክረምት መግባትን ተከትሎ በተሰራው ሥራ እስካሁን 500 ሺህ ሄክታር መሬት በሰሊጥና በአኩሪ አተር ሰብሎች በዘር መሸፈኑ ተመልክቷል።
በቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በክልሉ ለኢንዱስትሪ ግብአትና ለወጪ ንግድ የሚሆኑ ሰብሎችን ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው።
በዚህም በ2017/18 የምርት ዘመን 781 ሺህ ሄክታር መሬት በአኩሪ አተርና ሰሊጥ ሰብሎች ለመሸፈን ታቅዶ በተሰራው ስራ እስካሁን ድረስ 500 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ተችሏል ብለዋል።
ከዕቅዱ ጋር ሲነጻጸርም ያልታረሰ ቀሪ መሬት እንዳለ ገልጸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁሉንም መሬት በመዝራት ወደ አረምና እንክብካቤ ሥራ ለመግባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ የምርት ማሳደጊያ ግብአትና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአኩሪ አተርን አማካይ ምርታማነት በሄክታር ወደ 28 ኩንታል፤ ሰሊጥን ደግሞ ወደ ዘጠኝ ኩንታል ለማሳደግ ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው።
በአሁኑ ወቅት ያለው የዝናብ ስርጭት ለዘር ሥራና ለሰብል ልማቱ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ በመኸር እርሻ ለኢንዱስትሪዎች ግብአት እና ለውጪ ንግድ የሚሆን በቂ ምርት ለማምረት እንደሚያስችልም ገልጸዋል።
በአኩሪ አተርና ሰሊጥ ከሚለማው ሰብል ከ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ጥራቱን ጠብቆ ለማምረትና ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑንም ማንደፍሮ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
በምዕራብ ጎንደር ዞን በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩት ባለሃብት አቶ ሃብቱ ጽዱ በበኩላቸው እንዳሉት፣ 643 ሄክታር መሬት ገበያ ተኮር በሆኑ ሰብሎች በመሸፈን እያለሙ ይገኛሉ።በዚህም ሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ ሱፍ እና ጥጥ እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት የዘር ሥራቸውን አጠናቀው ወደ አረምና እንክብካቤ ሥራ መግባታቸውንና ከልማቱም የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።
በዘንድሮ የመኸር ወቅት ከአምስት ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥና አኩሪ አተር ሰብል ማልማታቸውን የገለጹት ደግሞ በዞኑ የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ አርሶ አደር ታደሰ አይናለም ናቸው።
የዝናብ ሥርጭቱ ለሰብል ልማቱ አመቺ ሁኔታን በመፍጠሩ የተሻለ ምርት አገኛለሁ ብለው እንዲጠብቁ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።
ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በ2016/2017 የምርት ዘመን በክልሉ በሰሊጥና በአኩሪ አተር ሰብል ከለማው መሬት 10 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ተሰብስቦ ለገበያ ቀርቧል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025