የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በዞኑ ሰላምን በማፅናት ለልማት ተግባራት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፣ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ጎንደር ዞን ሰላምን በማፅናት ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ተግባራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ጌትነት በዛ ለኢዜአ እንደገለጹት፤በየደረጃው የሚገኘው የዞኑ ሕዝብ የፅንፈኛውን ቡድን የጥፋት መንገድ አደባባይ ወጥቶ ከማውገዝ ባለፈ የህግ የበላይነት እንዲከበር የድርሻውን መወጣቱን ቀጥሏል።

ተከታታይ ህዝባዊ መድረኮች በመፍጠር ቡድኑን ከሕህዝቡ የመነጠል ስራ መከናወኑን አውስተዋል።

በዞኑ የሰፈነውን ሰላምና መረጋጋት በማስጠበቅ የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያግዙ ውጤታማ ሰራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።

መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ ወደ ሰላም የመጡ በርካታ ታጣቂዎችን የተሃድሶ ስልጠና በመውሰድ ሕብረተሰቡን በልማት እንዲክሱ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ፅንፈኛውን ቡድን ከዞኑ ለማፅዳት ከመከላከያ ሰራዊቱና ከሌሎችም የህግ አስከባሪዎች ጋር በመተባበር እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተዋል።

በተወሰደበት እርምጃ ፅንፈኛው እየታደከመ መምጣቱን ገልጸው፤ ይህም ለግብርና ልማቱ ግብአት ለማቅረብና ባለሙያዎች ተንቀሳቅሰው አርሶ አደሩን እንዲደግፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል።

ቀሪ የፅንፈኛውን ቡድን አባላት በየጊዜው የሰላም አማራጭን በመቀበል አሁንም እየተመለሱ መሆኑም አመልክተዋል።

የተገኘውን ሰላም በማፅናት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር አስቻይ መደላደል መፈጠሩን ኃላፊው አስታውቀዋል።

መንግስት አሁንም በሰላማዊ መንገድ ለሚመጡ ታጣቂዎች እጁ የተዘረጋ መሆኑን ጠቁመው፤ ይሄን በማይቀበሉት ላይ ደግሞ ከሕዝቡ ጋር በመተባበር የህግ ማስከበር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025