ባህር ዳር፣ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ጎንደር ዞን ሰላምን በማፅናት ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ተግባራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ ጌትነት በዛ ለኢዜአ እንደገለጹት፤በየደረጃው የሚገኘው የዞኑ ሕዝብ የፅንፈኛውን ቡድን የጥፋት መንገድ አደባባይ ወጥቶ ከማውገዝ ባለፈ የህግ የበላይነት እንዲከበር የድርሻውን መወጣቱን ቀጥሏል።
ተከታታይ ህዝባዊ መድረኮች በመፍጠር ቡድኑን ከሕህዝቡ የመነጠል ስራ መከናወኑን አውስተዋል።
በዞኑ የሰፈነውን ሰላምና መረጋጋት በማስጠበቅ የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያግዙ ውጤታማ ሰራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።
መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ ወደ ሰላም የመጡ በርካታ ታጣቂዎችን የተሃድሶ ስልጠና በመውሰድ ሕብረተሰቡን በልማት እንዲክሱ እየተደረገ ነው ብለዋል።
ፅንፈኛውን ቡድን ከዞኑ ለማፅዳት ከመከላከያ ሰራዊቱና ከሌሎችም የህግ አስከባሪዎች ጋር በመተባበር እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተዋል።
በተወሰደበት እርምጃ ፅንፈኛው እየታደከመ መምጣቱን ገልጸው፤ ይህም ለግብርና ልማቱ ግብአት ለማቅረብና ባለሙያዎች ተንቀሳቅሰው አርሶ አደሩን እንዲደግፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል።
ቀሪ የፅንፈኛውን ቡድን አባላት በየጊዜው የሰላም አማራጭን በመቀበል አሁንም እየተመለሱ መሆኑም አመልክተዋል።
የተገኘውን ሰላም በማፅናት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር አስቻይ መደላደል መፈጠሩን ኃላፊው አስታውቀዋል።
መንግስት አሁንም በሰላማዊ መንገድ ለሚመጡ ታጣቂዎች እጁ የተዘረጋ መሆኑን ጠቁመው፤ ይሄን በማይቀበሉት ላይ ደግሞ ከሕዝቡ ጋር በመተባበር የህግ ማስከበር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025