ሆሳዕና፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በየዘርፉ የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ።
"ከመስፈንጠር ከፍታ ወደ ላቀ እመርታ!” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የመንግሥትና የፓርቲ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ላይ ያተኮረ የአመራር ምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡
በመድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳመለከቱት፤ ባለፈው የበጀት ዓመት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተያዙ እቅዶችን በቅንጅት በመስራት ተስፋ ሰጪ ውጤት ተመዝግቧል፡፡
በዚህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኑሮ ውድነትን ከማረጋጋት ባሻገር በከተማና በገጠር መንገድ ተደራሽ እንዲሆን የተደረገውን ጥረት ጠቅሰዋል።
ለወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አንጻር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ይህም በክልሉ በበጀት ዓመቱ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ስራዎች በትክክለኛ መንገድ ላይ እንደሚገኙ አንስተዋል።
በተያዘው የበጀት ዓመት መልካም አስተዳደርን በማስፈን ፍትሀዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለተገልጋዩ ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ተናግረዋል።
የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል በየዘርፉ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ አመራሩ በቅንጅት መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)፥ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በፓርቲ ደረጃ ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በዚህም በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
ባለፈው የበጀት ዓመት የተስተዋሉ ውስንነቶችን በማረም የሕዝብ ተጠቃሚነትን ይበልጥ ለማጎልበት በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ እንዳሉት፤ በዞኑ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በግብርና ልማት፣ በንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና በሌሎችም ዘርፎች ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል።
በመድረኩ ላይ ካለፈው የስራ ዘመን እቅድ አፈጻጸም ሌላ የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ምክክር የተደረገ ሲሆን ፤ በዚህም የክልል፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025