አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፦በ2017 በጀት አመት ህብረተሰቡ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ገለፀ።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነባ መሆኑም ተገልጿል።
በ2017 በጀት ዓመት ህብረተሰቡ ለግድቡ ግንባታ ያደረገውን ድጋፍ፣ ትብብርና እገዛ በተመለከተ የጽህፈት ቤቱ ምክትል ስራ አስፈጻሚ ፍቅርተ ተአምር ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተፋሰሱ ሀገራት ህዝቦችን በጋራ የማደግ ትልምን የሚያሳካ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም መላው ኢትዮጵያውያን በሞራል፣ በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በፐብሊክ ዲፕሎማሲ እንዲሁም አካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ያሳኩት ዘመን ተሻጋሪ ስኬት መሆኑንም አስረድተዋል።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ አልፎ የአካባቢውን ሀገራት የኤሌትሪክ ሃይል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት መሆኑንም አክለዋል።
ምክትል ስራ አስፈፃሚዋ ከቦንድ ሽያጭና ስጦታ፣ ከዲያስፖራው ማህበረሰብ፣ ከ8100 A አጭር የፅሁፍ መልዕክት ድጋፉ መሰባሰቡንም ጠቅሰዋል።
በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለግድቡ ግንባታ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ገልጸው፤ ይህም ከዕቅዱ አንጻር የ7 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል፡፡
ህብረተሰቡ ያደረገው ድጋፍ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር አፈፃፀሙ የ21 በመቶ ብልጫ ማሳየቱንም ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025