ደሴ ፤ ሐምሌ 10/2017(ኢዜአ)፡-በደቡብ ወሎ ዞን በተያዘው የመኸር ወቅት ከ221 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ለማልማት የዘር ሥራ መጀመሩን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በስንዴ ከሚለማው መሬት ከዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል።
በዞኑ ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ፤ በዞኑ ያለው የአየር ንብረትና መልክአምድር ስንዴን በስፋት ለማምረት የተመቸ መሆኑን ለኢዜአ ተናግረዋል።
በዚህም በምርት ዘመኑ እርሻ ማሳውን ደጋግሞ በማረስና የግብዓት አቅርቦት ዝግጅት በማድረግ ከ221 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ ለማልማት የዘር ሥራ መጀመሩን አስታውቀዋል።
ከሚለማው መሬትም 145 ሺህ ሄክታር የሚሆነው በኩታ ገጠም ጠቁመው፤ ይህም ግብዓት ለማቅረብ፣ ለድጋፍ፣ በጋራ ለመዝራትና ተባይ ለመከላከል ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።
ከስንዴ ልማቱም ከዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸው፤ አርሶ አደሩ በምግብ ራሱን ከመቻል ባሻገር ለገበያ የሚቀርብ ትርፍ ምርት እንዲያመርት እየተበረታታ መሆኑን አመልክተዋል።
አርሶ አደር አሊ የሱፍ በዞኑ ከለላ ወረዳ የ02 ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ፤ ከአንድ ሄክታር የሚበልጥ መሬታቸውን በኩታ ገጠም ስንዴ ለማልማት የዘር ሥራ መጀመራቸው ገልጸዋል።
ለስንዴ ልማት በቂ ማዳበሪያ ከማግኘታቸው ባለፈ የግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ እያደረጉላቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህም የተሻለ በማምረት ከራሳቸው አልፎ ለገበያም ለማቅረብ እየሰራሁ ነው ብለዋል።
በግብርና ባለሙያ ታግዘው የስንዴ ዘር ሥራ መጀመራቸውን የተናገሩት ደግሞ በመቅደላ ወረዳ የ06 ቀበሌ አርሶ አደር አብዱ ኑርዬ ናቸው።
ከግማሽ ሄክታር በላይ መሬት በስንዴ በማልማት የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ባለፈ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት ጠንክረው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
የኩታገጠም ልማት ግብዓት ቅድሚያ ማግኘታቸው፣ በባለሙያ መደገፋቸውና በጋራ በመዝራት ሰብል መንከባከብ እንዲችሉ ምቹ መደላድል እንደፈጠረላቸው አርሶ አደሮቹ ተናግረዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን በ2017/2018 የመኸር ወቅት በአጠቃላይ 432 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብል በማልማት 15 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025