የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አምራቾች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት እያሳዩ ነው

Jul 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦ ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አምራችና ሻጭ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ምርታቸውን ለማቅረብና በዘርፉ በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ፍላጎት እያሳዩ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ገለፁ።

በየዓመቱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን የሚገጣጥሙና ለሽያጭ የሚያቀርቡ ተቋማት ቁጥር እያደገ መምጣቱንም ገልፀዋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን ለኢዜአ እንደገለጹት በአገሪቱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ለማስፋፋትና በዘርፉ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው።


የነዳጅ ኃይል ጥገኝነት ለመቀነስና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ዘርፉን አገሪቱ ካላት እምቅ የታዳሽ ሃይል ሀብት ተጠቃሚ ለማድረግ አበረታች ስራዎች መጀመራቸውን ተናግረዋል።

ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ተሽከሪካሪዎች ስትራቴጂን ተግባር ላይ በማዋል ተግባራዊነቱን ለማፋጠንና ኢንቨስትመንቱን ሳቢ ለማድረግ የሚረዱ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል።

መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኤሌክትሪክ የመቀየር እንዲሁም የነዳጅ አጠቃቀምንና ብክለትን በሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎች ላይ የሚሰሩ ስራዎችን እያበረታታ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በነዳጅ የሚሰሩ የቤት አውቶሞቢሎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ እገዳ መጣሉን አንስተው በአለም ገበያ ተደራሽ ያልሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎችና መሳሪያዎች በእገዳው አለመካተታቸውን ጠቅሰዋል።

በቅርቡ ከሁለት እግር ጀምሮ እስከ ከተማ አውቶብስ ያሉና በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ መገጣጠም መከልከሉን አንስተዋል።


በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሃብቶች የተለያዩ ማበረታቻዎች በፖሊሲ፣ ስትራቴጂና በመመሪያ ተደግፈው ተግባራዊ በመደረጋቸው በርካታ ውጤት ተገኝቷል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቁጥር ከ115 ሺህ በላይ እንዲሁም የኤሌክትሪክ ተሽከሪካሪ መገጣጠሚያ ድርጅቶች ቁጥር ከ15 በላይ መድረሱን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ ለዘርፉ የሰጠችውን ትኩረት ተከትሎ አሁን ላይ በርካታ ዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አምራቾችና ሻጮች በዘርፉ በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ሰፊ ፍላጎት እያሳዩ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በአሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚሰጥ የከተማ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎትን ለማስፋፋት የሚረዱ ስራዎች በመንግስትና በግል አጋርነት መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።

በአዲስ አበባ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ባትሪ መሙያ ቋሚ ጣቢያዎች ቁጥር ከ90 እንደማይበልጥ አንስተው ይህንን ለማሳደግ የመንግስት የልማት ድርጅቶችና የግል ባለሀብቶች በዘርፉ እንዲሰማሩ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025