ሐመር-ዲመካ፤ ሐምሌ 3/2017 (ኢዜአ)-በደቡብ ኦሞ ዞን አርብቶ አደሩ በራስ አቅም የምግብ ዋስትናውን የሚያረጋግጥበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
በዞኑ የ2017/18 ምርት ዘመን የመኸር እርሻ ንቅናቄና የአመራር አባላት የአቅም ግንባታ መድረክ በዞኑ በዲመካ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማሊኮ እንደገለጹት መንግስት በአርብቶ አደሩ አከባቢ የተረጅነት አመለካከትን በመቀየር ወደ ምርታማነት ለማሸጋገር ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎችን እያከናወነ ነው።
አርብቶ አደሩ ቀደም ሲል መተዳደሪያው በከብት እርባታ ላይ ብቻ የተመሰረተ መሆኑን አንስተው፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መንግስት በሰጠው ትኩረት ከከብት እርባታው ጎን ለጎን በመስኖ ልማት ተሳትፎ እንዲያደርግ እገዛ እያደረገ መሆኑን አንስተዋል ።
ዝናብ አጠር በሆኑ አካባቢዎች የመስኖ አውታሮችን በማስፋፋት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል ።
"በዚህም በዞኑ ባለፉት አመታት በተከናወኑ የግብርና ልማት ስራዎች አርብቶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን ከማረጋገጥ ባለፈ የኢኮኖሚ አቅሙን የሚያጎለብትበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል" ብለዋል።
አርብቶ አደሩ በመስኖ ልማት እያደረገ ያለው ተሳትፎ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ምንላርገው አዲሱ ናቸው።
በዞኑ በተከናወኑ የግብርና ልማት ስራዎች የተረጅነት አመለካከት እየተቀረፈ መምጣቱን ተናግረዋል ።
በአሁኑ ሰአት በዞኑ ሰፋፊ የግብርና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተው ጥጥ፣ ሙዝ፣ ማሾና ሰሊጥ የመሳሰሉ የግብርና ምርቶችንም ለማዕከላዊ ገበያ ከማቅረብ ባለፈ ወደ ጎረቤት ሀገራት ለገበያ እየተላኩ መሆኑን አስታውቀዋል ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025