አዲስ አበባ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ የሚደረጉ ትብብሮች እንዲሳለጡ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት ትሰራለች ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
በፎረሙ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀመድ አሊ የሱፍ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የአፍሪካ ሀገራት ሚኒስትሮች፣ የፈጠራ ባለሙያዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎችና የዘርፉ ምሁራን እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ፎረሙ አፍሪካ ያላትን እምቅ ሀብት ወደ ተጨባጭ አቅም ለመቀየር፣ ሥራ አጥነትን ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ፣ ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትንና አህጉራዊ ትስስርን ማላቅ ዓላማ አድርጎ ላለፉት ሁለት ተከታታይ ዓመታት ሲካሄድ ቆይቷል፡፡
ዘንድሮም ለሦስተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ከዛሬ ጀምሮ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በመካሄድ ላይ ሲሆን እስከ ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በኢትዮጵያ ለሥራ ዕድል ፈጠራ በተሰጠው ትኩረት በአማካኝ በየዓመቱ ለ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።
ለሥራ ፈጠራው ምቹ ሥነ ምህዳር የመፍጠሩ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም አንስተዋል።
ከግሉ ዘርፍ፣ ከሴክተር መስሪያ ቤቶችና ከቀጣናዊ የልማት አጋሮች ጋር የተፈጠረው የትብብር አውድ መልካም ውጤቶች እንዲገኙ ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ ነው ብለዋል።
ዛሬ መገናኘታችን በርካታ ፋይዳዎች አሉት ያሉት ሚኒስትሯ የጋራ እጣ ፈንታችንን በጋራ እና በህብረት ለመጻፍ መነሳት እንዳለብን የሚያመላክት ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ወቅቱ የሚጠይቀው አርበኝነት ጠንካራ የሥራ ባህል መገንባት በመሆኑ በትብብር መሥራት ይገባል ነው ያሉት።
በሥራ ዕድል ፈጠራ በኩል በአፍሪካ የሚደረጉ ትብብሮች እንዲሳለጡ ኢትዮጵያ በቁርጠኝነት እንደምትሰራም ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
በአፍሪካ በየዓመቱ 30 ሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ገበያውን የሚቀላቀሉ መሆኑን ጠቅሰው፤ እንዲያም ሆኖ በርካታ ተመራቂ ወጣቶች አሁንም ሥራ ይፈልጋሉ ብለዋል።
ሚኒስትር ሙፈሪሃት ክህሎትና ሥራ ዕድል ፈጠራዎች አሁንም ያልተሻገርናቸው የቤት ሥራዎች ናቸው ሲሉም አንስተዋል።
ፎረሙ በይፋ ሲጀመር እንደ አህጉር በሚቀጥሉት 15 ዓመታት ከ80 እስከ 125 ሚሊዮን ለሚደርሱ ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ግብ መያዙን አስታውሰው፤ ግቡ ብዙ ሥራ የሚጠይቅ ሆኖ በትብብርና በቁርጠኝነት ከተሰራ ሊሳካ የሚችል ነው ሲሉም አብራርተዋል።
በመድረኩ የግብርና እሴት ሰንሰለት፣ ዲጂታላይዜሽንና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ በተለይ ለሴቶችና ወጣቶች ምቹና አስተማማኝ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትስስርን ማላቅ ላይ ያተኮረ ምክክር ይደረጋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025