የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ ለድህነት ቅነሳ ተግባራትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት ይሰጣል-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

Jul 4, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሰኔ 26/2017 (ኢዜአ)፦በሲዳማ ክልል በድህነት ቅነሳ ተግባራት ላይ በማተኮር ገበያን ማረጋጋትና የሥራ ዕድል መፍጠር ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ገለጹ፡፡

ክልሉ የተመሰረተበትን 5ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል፡፡


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ ክልሉ በአዲስ መልክ ከተደራጀ በኋላ በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡

በዚህም የተመዘገቡ ስኬቶች እንዳሉ ገልጸው፣ የስኬቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ተሞክሮዎችን ማስፋት፣ ማነቆዎችን መፍታትና በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በቀጣይም ድህነትን በሚቀንሱ ተግባራት ላይ በማተኮር ገበያን ማረጋጋት፣ ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠርና የቤተሰብ ብልጽግናን ማረጋገጥ የክልሉ መንግስት ትኩረቶች መሆናቸውን አስረድተዋል።

ለዚህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአቅርቦት እጥረት ችግርን በመፍታት የእያንዳንዱን ቤተሰብ ህይወት ለመቀየር የተቀረጸውን ፓኬጅ በመተግበር የህብረተሰቡን ገቢ ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል፡፡

በክልሉ ለወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር የተገኙ ውጤቶች አበረታች መሆናቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳደድሩ፣ በቀጣይ ተጨማሪ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ ቀድመው ወደሥራ የገቡትን የመደገፍ ሥራ ይሰራል ብለዋል፡፡

መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የተጀመሩ ሥራዎች እያስገኙ ያሉትን ውጤት በማስቀጠል በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የህዝብን እርካታ ማረጋገጥ ሌላው ትኩረት መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በውይይት መድረኩ ከክልሉ መንግስት ዕቅድ ጋር የሚጣጣሙ ሀሳቦች መንጸባረቃቸውን ገልጸው፣ የክልሉን እድገት ለማፋጠን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት ይሰራል ብለዋል።

የክልሉን የአምስት ዓመታት ጉዞ ሰነድ ለውይይት ያቀረቡት የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ አራርሶ ገረመው (ዶ/ር) በበኩላቸው በመሰረተ ልማት ዘርፍ የተከናወኑ ሥራዎች ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ የሰጡ ናቸው ብለዋል።


በዚህም ባለፉት አምስት ዓመታት ከ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ከ1 ሺህ 400 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የክልሉን የመጠጥ ውሃ ሽፋኑን ወደ 64 በመቶ ያሳደጉ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት መብቃታቸውንም ተናግረዋል፡፡

በትምህርት ዘርፍም ቅድመ መደበኛ ላይ ትኩረት በማድረግ ባለሃብቱንና ህዝቡን በማስተባበር የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ መከናወኑን ገልጸው፣ በዚህም ከፍተኛ ለውጥ መታየቱንም ጠቁመዋል፡፡

አራርሶ (ዶ/ር) እንዳሉት በግብርና፣ በእንስሳትና ዓሣ ሃብት ልማት ምርታማነትና ገቢን ለማሳደግ የተሰሩ ሥራዎችም በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ድርሻ አላቸው፡፡

የሲዳማ ክልል ከተደራጀ በኋላ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎችና በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ዓመታት የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ትናንት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተጎብኝተዋል።

በዛሬው መድረክም በመስክ ምልከታ በታዩ ጉዳዮችና በቀረበው ሰነድ ላይ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በጋራ መክረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025