አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ):-ኢትዮጵያ መለመን የለባትም፤ልጆቿ ተግተው ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፥ አምርታ መብላት የማትችል ሀገር ብሄራዊ ጥቅሞቿን ለማሳካት እንድምትቸገር ገልጸዋል።
ምርት ከማምረት እና ከመሸጥ ባለፈ በግብርና እሴት ሰንሰለት ውስጥ ያሉ ጉዳዮች ላይ ሁሉን አቀፍ መፍትሄ ማምጣት የምግብ ሉዓላዊነትን ለማምጣት ያስችላል በሚል እሳቤ ሲከናወኑ የቆዩ ስራዎች ውጤት ማስገኘታቸውን አመልክተዋል።
ባለፉት ዓመታት 27 ሚሊዮን ዜጎች በሴፍቲኔት ኢኒሼቲቭ በተረጂነት ማዕቀፍ ውስጥ እንደነበሩ አስታውሰዋል።
መንግስት ዜጎችን ከሴፍቴነት ነጻ ለማውጣት በግብርናው ንዑስ ዘርፍ ትኩረት ተሰጥቷቸው ሲሰሩ ከነበሩ ጉዳዮች መካከል አንዱ እንደሆነ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በምስራቅ ሐረርጌ እና በደቡብ ሃላባ በነበራቸው ቆይታ አርሶ አደሮች ከሴፍቲኔት ተላቀው በራሳቸው አቅም ማምረት መጀመራቸውን እንደተመለከቱ አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ መለመን የለባትም ልጆቿ ተግተው ሰርተው ከልመና ራሳቸውን መገላገል አለባቸው የሚለው እምነት ፍሬ እያፈረ መምጣቱን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹት።
ዘንድሮ 23 ሚሊዮን ዜጎች ከሴፍቲኔት ተረጂነት ነጻ ወጥተዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ይህ የማንሰራራት እና ኢትዮጵያ ከጥገኝነት ለመላቀቅ የጀመረችው ስራ ትልቁ ማሳያ ነው ብለዋል።
በቀጣይ የኢትዮጵያን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ የጋራ ጥረት እና ርብርብ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025