የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በዓለም ላይ የሚስተዋሉ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን መቋቋምና ምላሽ መስጠት የሚችሉ ጠንካራ ተቋማትን መፍጠር ይገባል

Jun 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2017(ኢዜአ)፦ በዓለም ላይ የሚስተዋሉ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን መቋቋምና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችሉ ጠንካራ ተቋማትን መፍጠር እንደሚገባ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ገለጹ።

ኢትዮጵያ ከሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት በትይዩ ያስተናገደቻቸው 10ኛው የአፍሪካ ሕብረት አባል ሀገራት የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር እና የተመድ የአፍሪካ ቀጣናዊ ፎረም ዛሬ ተጠናቀዋል።


የመንግሥት ተቋማት ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን ተቋቁመውና በየዘመኑ እየተንከባለሉ የመጡ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በመፍታት አካታች፣ ዘላቂ ልማት የሚያመጣ ተጠያቂነትን የሚያሰፍን፣ ሰብዓዊ መብት የሚያከብር፣ የህዝቦችን ትብብር የሚያጠናክሩ ተቋማትን ለመፍጠር ያለመ ነበር።

አቶ አደም ፋራህ በማጠቃለያ መርሀ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በትይዩ የተካሄዱት ሁለቱም መድረኮች በስኬት መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል።

በዓለም ላይ እየተስተዋሉ ያሉ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን መቋቋምና ቀድሞ ምላሽ መስጠት የሚችሉ ጠንካራ ተቋማትን መፍጠር ይገባል ብለዋል።

በመሆኑም ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ያለውን ውስብስብነት ከግምት ያስገቡ አዳዲስ ፈጠራዎችና ሞዴሎችን ገቢራዊ ማድረግ ይገባል ነው ያሉት።

የመንግሥት አገልግሎት በአፍሪካ ለዘመናት የቆዩ ችግሮችን መፍታት የሚያስችል መሆኑን በመጥቀስ፤ በአገልግሎት ሰጪዎች ላይ የክህሎት፣ የአመራር እና የትብብር አቅምን ማጎልበት ለሀገራዊ ሽግግር ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።

የኮንፍረንሱ ዓላማ የተቋም ግንባታ ብቻ ሳይሆን ለዜጎች ግልፅና ቀልጣፋ አገልግሎት የመስጠት ሀላፊነት ጭምር መሆኑን ተናግረዋል።

የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ፅንሰ ሀሳብ ለዜጎች ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት የመነጨ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁን ባለው ሂደት ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሪፎርም ከአፍሪካ ሕብረት አጀንዳ 2063 እና የተመድ 2030 ዘላቂ የልማት ግቦች ጋር የተሰናሰነ መሆኑን አንስተዋል።

ስብሰባው የመንግሥት አሰራርን በቴክኖሎጂ መደገፍ፣ የሰው ሀይል አስተዳደርንና የኢኖቬሽን አገልግሎትን ማቀላጠፍ ዘመኑ የሚጠይቀውን ተቋም ለመፍጠር ያግዛል ብለዋል።

ከዚህም ባለፈ ጠንካራ ተቋማዊ አደረጃጀት በመፍጠር ተቋማዊ ተጠያቂነትን ማስፈንና የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ ልምዶች የተገኙበት መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025