አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2017(ኢዜአ)፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በጎንደር ከተማ በከፊል የተጣራ የአኩሪ አተር ዘይት የሚያመርተውን የቲቲኬ ኢንደስትሪን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ለመጎብኘት ጎንደር ከተማ ገብተዋል።
ጎንደር አፄ ቴዎድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የከተማዋ ህዝብ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በከተማዋ በከፊል የተጣራ የአኩሪ አተር ዘይት የሚያመርተውን የቲቲኬ ኢንደስትሪን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።
ኢንደስትሪው በ374 ሚሊዮን ብር የተገነባ ሲሆን በቀን 120 ቶን የአኩሪ አተር ዱቄት እና በከፊል የተጣራ የምግብ ዘይት የማምረት አቅም እንዳለውም ተገልጿል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቲቲኬ ኢንደስትሪ ፋብሪካ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለጀመርነው የአምራች ኢንዱስትሪ ልማት አንድ ሁነኛ አብነት ነው ብለዋል።
ጎንደር ሰላምን በማስጠበቅና በማጽናት ልማትን የማረጋገጥ ለዕድገትም የመትጋት ደማቅ ማሳያ እንደሆነች ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025