የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

በአማራ ክልል የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ የሚያጠናክሩ ተግባራት ትኩረት የተሰጣቸው ናቸው- ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ

May 25, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብርናውን ክፍለ ኢኮኖሚ የሚያጠናክሩ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ አስታወቁ ።

የጎንደር የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የግንባታ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት በጎንደር ዙሪያ ወረዳ ዛሬ ተካሂዷል ።

ርእሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚያጠናክሩና የሚያሳልጡ ተግባራት ትኩረት የተሰጣቸው ናቸው ።


በክልሉ ግንባታው የተጀመረው የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የዚሁ አካል መሆኑን ጠቁመው ፓርኩ በክልሉ ዋነኛ የኢኮኖሚ ማእከል እንደሚሆንም አመልክተዋል ።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በበኩላቸው በሀገሪቱ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር በማፋጠን ረገድ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወሳኝ የእድገት ምሰሶዎች ናቸው ብለዋል።

የተቀናጀ የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የግብርና ምርት እሴት ጨምሮ ለሀገርና ለውጪ ገበያ ለማቅረብ ምቹ የኢኮኖሚ መሠረት የሚጥሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ዛሬ ግንባታው የተጀመረው አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ የአካባቢውን የግብርና ምርት በስፋት በመጠቀም ለአካባቢው አምራች አርሶ አደሮች ሰፊ የገበያ እድል የሚፈጥር እንደሆነም አመልክተዋል።

ፓርኩን በሂደት ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን በማሳደግ እንደ ሀገር ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገውን ሽግግር ለማሳለጥ ምቹ መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰዋል።

ፓርኩ ለግብርና ምርቶች የገበያ እድል በማመቻቸት ለወጣቶች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር እንዲሁም ለከተሞች ገቢ ማደግና ለቴክኖሎጂ ሽግግር የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለውም ጠቁመዋል።

የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሀኑ ጣምያለው ኢንዱስትሪ ፓርኩ በ256 ሄክታር መሬት ላይ ግንባታው እንደሚካሄድ ገልጸዋል።


የፓርኩ ግንባታ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ የኢንቨስትመንት ወጪ እንደሚጠይቅ ጠቁመው ስራ ሲጀምር ለ55 ሺህ ወገኖች ቋሚ እንዲሁም ከ200ሺህ በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ጊዚያዊ የስራ እድል ይፈጥራል ብለዋል።

ፓርኩ በአመት ከአንድ ሚሊዮን ቶን በላይ ምርት የማቀናበር አቅም ሲኖረው እሴት የተጨመረባቸውን ምርቶች ለውጪ ገበያ በማቅረብ የውጪ ምንዛሪ የሚያስገኝ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የማእከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ ዞኑ ለአግሮ ኢንዱስሪዎች ግብአት የሚውል ሰሊጥ፣ አኩሪ አተርና ጥጥ የመሳሰሉ የግብርና ምርቶች በስፋት የሚመረቱበት እንደሆነ ተናግረዋል ።


ኢንዱስትሪ ፓርኩ ለአካባቢው የኢኮኖሚ መነቃቃት አስተዋፅኦው የላቀ መሆኑንም አመልክተዋል።

በኢንዱስትሪ ፓርኩ የግንባታ ማስጀመሪያ ስነ ስርአት ላይ የፌደራል፣ የክልል እንዲሁም የጎንደር ከተማና የማእከላዊ ጎንደር ዞን አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ ነው-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2018 (ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መመረቅ ፍትሐዊና ሚዛናዊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታን የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቅላ...

May 28, 2026

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026