የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

የትውልድ አጀንዳ የሆነውን የባሕር በር ጥያቄ ለማሳካት ወጣቶች በዕውቀትና በንቃት መሳተፍ አለባቸው-የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን

Apr 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርና የትውልድ አጀንዳ የሆነውን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ከግብ ለማድረስ ወጣቶች በዕውቀትና በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ገለጸ።

የኢትዮጵያን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ዘላቂ ለማድረግና እየጨመረ የመጣውን የሕዝብ የልማት ፍላጎት ለማሟላት አስተማማኝ የባሕር በር ማግኘት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።

ይህንን ብሔራዊ ግብ ለማሳካትም፣መንግሥት ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት እንድትሆን የሚያስችሉ ውጤታማ የዲፕሎማሲ ሥራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን ዓለም አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አምባሳደር አሌክሳንደር ንጉሴ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ የባሕር በር መኖር ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ዕድገት ወሳኝ ነው።

አምባሳደር አሌክሳንደር አክለውም መንግሥት የባሕር በርን በሚመለከት ለሚያከናውናቸው ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ስኬታማነት ፌዴሬሽኑ የበኩሉን ሚና ለመወጣት እየሠራ መሆኑን አመልክተዋል።

የወጣቶችን ግንዛቤ የሚያጎለብቱ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ጠቁመው፣የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳን በዘላቂነት ለማሳካት ትውልዱ ትልቅ ኃላፊነት እንዳለበት ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርና የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ከግብ ለማድረስ ወጣቶች በዕውቀትና በንቃት ሊሳተፉ እንደሚገባ ገልጸዋል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች በበኩላቸው፣ የባሕር በር ጥያቄ የትውልዱ አጀንዳ መሆኑን ገልጸዋል።


ወጣት አቤኔዘር ኤርሚያስ የባሕር በር ጥያቄያችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እያገኘ መሆኑን ጠቅሶ፥ አሁንም ተፅዕኖ ፈጣሪ ወጣቶችን በመጠቀም አጀንዳውን ለዓለም ይበልጥ ማስገንዘብ አለብን ብሏል።

ወጣቶች በማህበራዊ ሚዲያ አጫጭር ቪዲዮዎችንና የታሪክ ማጣቀሻዎችን በመጠቀም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ተገቢነት ከሕጋዊ፣ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ አውዶች አንጻር ማሳወቅ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሷል።


በተመሳሳይ ወጣት ሩት ሸዋንቅጣውና ፌቨን ፍቃዱ የባሕር በር ጉዳይ የመንግሥት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ዜጋ ጉዳይ እንደሆነ አንስተዋል።


ወጣቱ ሐሳቡን በመግለጽና መንግሥትን በመደገፍ ረገድ ግንባር ቀደም ሚና ሊኖረው እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026