🔇Unmute
ባህር ዳር ፤ መጋቢት 13/2018 (ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል የግብይት ማዕከላትን በማስፋፋትና የንግድ ሰንሰለትን በማሳጠር የዋጋ ንረትን ለማርገብ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።
በአማራ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ እና በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የበጀት ድጋፍ የተገነባው የባህር ዳር ከተማ 2ኛ ደረጃ ዘመናዊ የገበያ ማዕከል ዛሬ ተመርቋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ የገበያ ማዕከላትን በማስፋፋት የዋጋ ንረትን ለመከላከል አቅጣጫ ተቀምጦ በትኩረት እየተሰራ ነው።
የገበያ ማዕከላት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት እንዲያካሄድ የሚያስችሉ በመሆናቸው የማስፋፋት ስራ ልዩ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ነው ሲሉ አክለዋል።
የገበያ ማዕከላት አምራቹንና ሸማቹን ቀጥታ በማገናኘት ከደላላ ጣልቃ ገብነት የጸዳ የግብይት ስርዓት ለማዳበር ሚናቸው የጎላ መሆኑን አመልክተዋል።

በክልሉ በርካታ የግብርና ምርት ማዕከላት እየተገነቡ መሆኑን ገልጸው ተግባሩን አጠናክሮ በማስቀጠል የዋጋ ንረትን የማርገብ ስራ በልዩ ትኩረት ይከናወናል ብለዋል።
በባህር ዳር ከተማ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት በሆነው የገበያ ማዕከል የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቾች እንደሚቀርቡ ታውቋል።
በምረቃ ስነ-ሥርዓቱ ላይ የክልሉና የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር አመራር አካላትና አምራቾች ተገኝተዋል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025