🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት ሰባት አመታት (ከ2010 - 2017 ዓ.ም) በፊስካል ፖሊሲና በመንግስት ፋይናንስ ረገድ ስኬቶች መመዝገባቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ እንዳመለከተው የመንግሥት የበጀት ጉድለትን ለመቀነስ በተወሰደው ርምጃ ከሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርት -2 ነጥብ 5 በመቶ የነበረው የበጀት ጉድለት ወደ -0 ነጥብ 9 በመቶ ዝቅ ብሏል።
የመንግስትን ገቢ የሚያሻሽሉ ሪፎርሞች ተግባራዊ በመደረጋቸው ጠቅላላ ገቢው ከ5 እጥፍ በላይ አድጓል።

የመንግስት የወጪ አቅጣጫው ድህነትን ለመዋጋትና ልማትን ለማረጋገጥ እንዲውል በመደረጉም ድህነት ተኮር ወጪ ከ5 እጥፍ በላይ አድጓል።
የበጀት ተዓማኒነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ የመካከለኛ ዘመን የፊስካል ማዕቀፍ እንዲጠናከር በመደረጉ የበጀት አፈጻጸሙ ተሻሽሏል።
ከብሔራዊ ባንክ የሚወሰደው ቀጥታ ብድር እንዲቀር በመደረጉ የዋጋ ንረትን ለመግታት አስተዋጽኦ አድርጓል።
መንግሥት የተቀናጀ የፋይናንስ አስተዳደር የመረጃ ስርዓት መዘርጋቱን ገልጾ፤ የዲጂታል ክፍያ አማራጮችን በመተግበር የፋይናንስ ስርዓቶችን በማዘመን የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓት ማዘመን እንደተቻለ ገልጿል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025