🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሁን እየተጠቀመበት ያለውን የተሽከርካሪ ታርጋ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን ባካተተ አዲስ ታርጋ ሊቀይር መሆኑን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል አስታወቁ።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወር የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሂዷል።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንደተናገሩት ፖሊስ አሁን እየተጠቀመባቸው ያሉ የተሽከርካሪ ታርጋዎችን ሙሉ በሙሉ በመቀየር አዳዲስና ዘመናዊ ታርጋዎችን በቅርቡ ስራ ላይ ለማዋል ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል።
ይህም ተቋሙ የወንጀል መከላከልና ምርመራ ስራውን በዘመናዊ መንገድ ለመምራት ከጀመራቸው የሪፎርም ስራዎች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።

አዲሱ ታርጋ የረቀቁ የቴክኖሎጂ ቁልፎች ያሉት ሲሆን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስን ብቻ የሚወክል፣ የተቋሙን የሙያ ብቃት እንዲሁም የዲሲፕሊን ደረጃ የሚያንፀባርቅ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮሚሽነር ጀነራሉ አዲሱ ታርጋ ታትሞ በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በይፋ ጥቅም ላይ እንደሚውል አረጋግጠዋል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025