🔇Unmute
ገንዳውኃ፤ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦በምዕራብ ጎንደር ዞን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን ለማነቃቃት እየተሰራ መሆኑን የዞኑ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ።
አበዳሪ ተቋማትን፣ የኢንቨስትመንት ፎካሎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈና ዘርፉን ለማነቃቃት ያለመ የምክክር መድረክ በገንዳውኃ ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።
በዞኑ የኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ መሰንበት መልካሙ እንደገለጹት በዞኑ በጸጥታ ችግር ምክንያት ተቀዛቅዞ የቆየውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማነቃቃት እየተሰራ ነው።
ዞኑ ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ ሰፋፊ መሬትና ተስማሚ የአየር ንብረት እንዳለው ገልፀው የዛሬው መድረክም በአካባቢው የሰፈነውን ሰላም ተከትሎ አዳዲስ አልሚዎችን ለመሳብና ነባር ኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማነቃቃት የብድር አቅርቦትና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት በማለም መሰናዳቱን አብራርተዋል።
የገንዳ ውኃ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ተወካይ ኃላፊ አቶ ታድሎ አቡሃይ እንዳሉት በከተማው 134 ሄክታር የሚጠጋ ቦታ ለኢንዱስትሪ ፓርክ ተለይቶ መሰረተ ልማት የማሟላት ስራ ተሰርቷል።
እስካሁን ከ14 በላይ የሚሆኑ ባለሀብቶች ማሸነሪ በመትከል እየሰሩ እንደሚገኙ ጠቁመው ወደ ስራ ያልገቡትን በመደገፍ ወደ ተግባር ለማስገባት ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።
በምዕራብ ጎንደር ዞን የዋሊያ ካፒታል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ብርሃኑ ስመኘው በበኩላቸው በዞኑ የሚካሄደውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለመደገፍ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ለአልሚ ባለሃብቶች የግብርና ግብዓቶችን፣ የሰሊጥ ማበጠሪያና ዘመናዊ መውቂያ ማሽኖች እየቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመው በቀጣይም ፍላጎትን መሰረት ያደረገ የካፒታል እቃዎች ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የገንዳውኃ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ደመወዝ ምትኩ በበኩላቸው የአካባቢውን ፀጋ ለማልማትና ሰፊ የስራ እድል ለመፍጠር ብድር በማቅረብ እየሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በውይይቱ ላይም አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸውም ተመልክቷል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025