🔇Unmute
አምቦ፤ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ) ፡- በምዕራብ ሸዋ ዞን በመኸሩ ከ31 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ለምቶ የደረሰ ሰብል በመሰብሰብ ላይ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በጽህፈት ቤቱ የአፈር ልማት ማሻሻያ ቡድን መሪ አቶ ተክሌ ኢዶሳ ለኢዜአ በሰጡት ማብራሪያ የመኸሩ የግብርና ልማት በጥሩ ሁኔታ ላይ በመሆኑ የተሻለ ምርት የሚጠበቅበት ነው ብለዋል።

በዞኑ 31 ሺህ 28 ሄክታር መሬት ላይ የለማውና የደረሰው ሰብል አሁን በመሰብሰብ ላይ መሆኑን አንስተው ከዚህም ከ938 ሺህ 490 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
በመኸሩ የስንዴ፣ ገብስ፣ ባቄላ፣ ቦሎቄና ሌሎችም ሰብሎች በመድረሳቸው በመሰብሰብ ላይ መሆናቸውን ገልጸው ከሰብል ስብሰባው ጎን ለጎን የአፈሩን እርጥበት በመጠቀም ዳግም የማልማት የዝግጅት ስራ የተጀመረባቸው አካባቢዎች አሉ ብለዋል።
የመኸር ምርቱ በተሰበሰበባቸው አካባቢዎችም እስካሁን ከ6 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች የመሸፈን ስራ መከናወኑን ገልጸዋል።
የተሰበሰበውን ሰብል ማሳ እርጥበቱ ሳይጠፋ ዳግም በዘር የመሸፈን ስራው ውጤታማ እንዲሆን ዘመናዊ ማረሻዎች ተሰራጭተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መደረጉንም አስረድተዋል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025