🔇Unmute
ባሕርዳር ፤ ጥቅምት 4/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ የመንገድ ግንባታና ጥገና ስራዎች ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ አስታወቀ።
በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎችን በማከናወን የልማት ትስስሩንና የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ይገኛል።
የአማራ ክልል ገጠር መንገዶች ኮንስትራክሽን ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ቀለሙ ሙሉነህ በተለይ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት በ34 ፕሮጀክቶች ከ102 ኪሎ ሜትር በላይ የአዳዲስ መንገዶች ግንባታ እንዲሁም የ6 ሺህ 38 ኪሎ ሜትር የነባር መንገዶች ጥገና ለማድረግ ታቅዷል።
ለዚህም ከክልሉ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር እና ከፌዴራል መንገድ ፈንድ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ደግሞ ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞ የመንገድ ግንባታ ስራዎች ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በመንገድ ግንባታው የ91 አነስተኛ፣ መካከለኛና ከፍተኛ ድልድዮች ግንባታ የሚካሄድ መሆኑን ጠቁመው፤ መሰረተ ልማቱ ዞን፣ወረዳና ቀበሌዎችን የሚያገናኝ ይሆናል ብለዋል።
በግንባታው ከ20 ሺህ 200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025