የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ጅግጅጋ ለሶማሌ ክልል ከተሞች ሞዴል በሚሆን መልኩ ሰፊ የልማት ጎዳና ላይ ትገኛለች - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Jul 31, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 23/2017(ኢዜአ)፦ ጅግጅጋ ለሶማሌ ክልል ከተሞች ሞዴል በሚሆን መልኩ ሰፊ የልማት ጎዳና ላይ እንደምትገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች የጅግጅጋ ከተማን የኮሪደር ልማት ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት የጅግጅጋ ከተማ የኮሪደር ልማት የምስራቋን ኮከብ ወርቃማ የውበት ደባብ አልብሷታል ብለዋል።


በከተማዋ በምሽት ተዘዋውረው ባደረጉት ምልከታ ከስምንት ወራት በፊት በሁለት ምዕራፍ የተጀመሩ ስራዎች በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ መሆናቸውን መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።

የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን የአስፋልት መንገዶች ያሰፋ፣ የእግረኛ እና የብስክሌት መንገዶችንም ያካተተ መሆኑን አድንቀው፥ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች ትኩረት እንደተሰጣቸውም ገልጸዋል።

የወጣቶችና ታዳጊዎች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች፣ የተሽከርካሪ ማቆሚያ፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኃይል መሙያ ጣቢያዎችም በመገንባት ላይ ናቸው ብለዋል።

ከተማዋ ለክልሉ ከተሞች ሞዴል በሚሆን መልኩ ሰፊ የልማት ጎዳና ላይ መሆኗንም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሱት።

የከተማዋ የቆየ ችግር የነበረውን ጎርፍ መከላከል የሚያስችሉ ማፋሰሻዎች፤ የተቀናጀ የውሃ፣ የመብራት፣ የቴሌኮምና የመንገድ መሠረተ ልማት ዝርጋታዎች የሚያበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በአጠቃላይ በከተማዋ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎች ባለሀብቶች በከተማዋ በሆቴል አገልግሎትና ሌሎች ዘርፎች ተሰማርተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታን እየፈጠሩ ይገኛሉም ነው ያሉት።

በጅግጅጋ ከተማ በሁለት ምዕራፍ የ30 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለማከናወን ታቅዶ ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.