አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 20/2017(ኢዜአ)፦የሁለተኛው የተመድ የምግብ ስርዓት ጉባዔ ተሳታፊዎች ማዕከሉን መጎብኘታቸው ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ ደቻሳ ገለጹ።
በኢትዮጵያ፣ በጣልያን እና በተመድ ትብብር የተዘጋጀው ሁለተኛው የተመድ የምግብ ስርዓት ጉባኤ እስከ ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ከተለያዩ አገራት የመጡና የሁለተኛው የመንግስታቱ ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባኤ ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከልን ጎብኝተዋል።
የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ ደቻሳ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢኒስቲትዩት ስር ከሚገኙ 22 የምርምር ማዕከላት አንዱ ነው።
የምርምር ማዕከሉ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እያደረገች ያለውን ጥረት ከዳር ለማድረስ ዓይነተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።
የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ እንደገለጹት፤ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባኤ መነሻነት ማዕከሉ መጎብኘቱ በግብርናው ዘርፍ የሚደረገውን ትብብር ያጠናክራል።
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፦ የሲሚንቶ ንግድ እና መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎችን በተመለከተ የወጡ መመሪያዎች ገበያውን በማረጋጋትና የዋጋ ግሽበትን በመቀ...
Feb 12, 2025