
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 20/2017(ኢዜአ)፦የሁለተኛው የተመድ የምግብ ስርዓት ጉባዔ ተሳታፊዎች ማዕከሉን መጎብኘታቸው ትብብርን ለማጠናከር ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ ደቻሳ ገለጹ።
በኢትዮጵያ፣ በጣልያን እና በተመድ ትብብር የተዘጋጀው ሁለተኛው የተመድ የምግብ ስርዓት ጉባኤ እስከ ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ከተለያዩ አገራት የመጡና የሁለተኛው የመንግስታቱ ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባኤ ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከልን ጎብኝተዋል።
የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ ደቻሳ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የመልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢኒስቲትዩት ስር ከሚገኙ 22 የምርምር ማዕከላት አንዱ ነው።
የምርምር ማዕከሉ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እያደረገች ያለውን ጥረት ከዳር ለማድረስ ዓይነተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።
የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሴ እንደገለጹት፤ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባኤ መነሻነት ማዕከሉ መጎብኘቱ በግብርናው ዘርፍ የሚደረገውን ትብብር ያጠናክራል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025