
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 7/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ ኤክስፖርት እና ኢምፖርት ባንክ(አፍሪ ኤግዚም ባንክ) ለአፍሪካን የልማት እና ትስስር ፕሮጀክቶች የሚያደርገውን ድጋፍ በተጠናከረ መልኩ መደገፉን እንደሚቀጥል አስታወቀ።
47ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት እና 7ኛው የህብረቱ ቀጣናዊ ማህበረሰቦች የመንፈቅ ዓመት የጋራ የትብብር ስብሰባ በኢኳቶሪያል ጊኒ ማላቦ ተካሂዷል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ ከስብሰባው ጎን ለጎን ከተሰናባቹ የአፍሪካ ኤክስፖርት እና ኢምፖርት ባንክ(አፍሪ ኤግዚም ባንክ) ተሰናባች ፕሬዝዳንት እና የቦርድ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር ቤኔዲክት ኦርማህ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይቱ የአፍሪካ ህብረት እና የአፍሪ ኤግዚም ባንክ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለማጎልበትና ባንኩ ለአፍሪካ ልማት እና ትስስር የሚያደርገውን ድጋፍ የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
ሊቀ መንበሩ ባንኩ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን መከላከልን ጨምሮ ለአፍሪካ ህብረት አባል ሀገራትና ለኮሚሽኑ እያደረገ ያለውን ዘላቂ ድጋፍ አድንቀዋል።

በተጨማሪም ሊቀ መንበሩ ከአዲሱ የባንኩ ፕሬዝዳንት ጆርጅ ኢሎምቢ(ዶ/ር) የተወያዩ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው ማረጋገጣቸውን ኢዜአ ከህብረቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025