የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በአዲሱ በጀት አመት ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠናክሮ ይቀጥላል- የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Jul 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 6/2017(ኢዜአ)፦በ2018 በጀት አመት ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ተናገሩ።

የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የኢንተርፕራይዞች ምስረታ እና የሰልጣኞች ምዝገባ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ተግባራዊ የማድረግ ሥራ እንደሚቀጥልም ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የዘርፉ የክልልና ከተማ አስተዳደር አመራሮች የኢንተርፕርነርሺፕ ስልጠና እና ዓመታዊ የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተካሂዷል።



በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊዎች፣ የፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲኖች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ እንደተናገሩት፤ ባለፉት አመታት በተቋም ግንባታ፣ በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በአሠሪና ሠራተኛ አበረታች ተግባራት ተከናውነዋል።

የተቋም ግንባታው ሀገር የጀመረችውን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በሚችል መልኩ መገንባቱን ጠቅሰው፤ የአሠራር ሥራዓቶችን የማሻሻል እና በቴክኖሎጂ የማዘመን ሥራም በትኩረት መሠራቱን ገልጸዋል።

ይህም በ2018 በጀት አመት ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ሚኒስትሯ ያስታወቁት።

በክህሎት ልማት ረገድም በተጠናቀቀው በጀት አመት አበረታች ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ጠቅሰው፤ የሰው ሀብት ልማት ሥራም ገበያ እና ፍላጎትን መሠረት በማድረግ መሰራቱን ተናግረዋል።

የሥራ እድል ፈጠራ ቁጥር ሪፖርት ጥራቱን የጠበቀ ለማድረግም የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት ተግባራዊ መደረጉን ገልጸዋል።

ህጋዊ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን ተግባራዊ ለማድረግ፣ ለኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር ለመፍጠርና ፋይናንስን ጨምሮ አስፈላጊ መንግስታዊ ድጋፎችን ለማቅረብ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።

በ2018 በጀት አመት ሁሉም የዘርፉ ተቋማት የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የኢንተርፕራይዞች ምስረታ እና የሰልጣኞች ምዝገባ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት የማካሄድ ሥራን አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ሚኒስትሯ አስገንዝበዋል።

በሀገር ውስጥ፣ በውጭ ሀገር እና በርቀት ሥራ ዕድል ፈጠራ አበረታች ስራዎች መሰራቱን ጠቅሰው፤ በአዲሱ በጀት አመትም የበለጠ ስኬት ለማስመዝገብ ርብርብ እንደሚደረግ አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.