
አዳማ፤ሰኔ 30/2017 (ኢዜአ):- የኦሮሚያ ክልል መንግስት ለህዝቡ የልማት ጥያቄዎች ምላሽ በሚሰጡ ስራዎች ላይ በማተኮር እየሰራ መሆኑን በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ገጠር ክላስተር አስተባባሪ አቶ አዲሱ አረጋ ገለፁ።
በአዳማ ከተማ አስተዳደር 171 ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት በቅተዋል።

ዛሬ ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል የዶሮና የወተት ላሞች እርባታ ማዕከላት፣ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤቶች፣ የአዳማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህንፃና የአስተዳደር ህንፃዎች፣ የፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ ማጠራቀሚያና መልሶ መጠቀሚያ ማዕከል፣ የመኖ ማቀነባበሪያ እንዲሁም የጎጆ ኢንዱስትሪዎች ይገኙበታል።
በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ገጠር ክላስተር አስተባባሪ አቶ አዲሱ አረጋ፤ ''የማንሰራራት ዘመን ላይ ሆነን የማይቻሉ የሚመስሉ የልማት ፕሮጀክቶችን እውን እያደረግን ነው'' ብለዋል።

የክልሉ መንግስት ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ፣ ፍጥነትና ጥራት አጠናቆ ለአገልግሎት እያበቃ መሆኑን ጠቅሰው የክልሉ መንግስት የህዝብ የልማት ጥያቄ ለመመለስ ልዩ ትኩረት ስጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የልማት ፕሮጀክቶችን በፍጥነት በማጠናቀቅና ለአገልግሎት ክፍት ከማድረግ ባለፈ አገልግሎት አሰጣጥን የማዘመን ስራ ጎን ለጎን እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱም የክልሉን ህዝብ፣ ባለሃብቶችና የተለያዩ አጋር አካላትን ጨምሮ የመንግስትን አቅም አንድ ላይ በማቀናጀትና በመጠቀም ስፋፊ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
አሁን እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶችን በማጠናከር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ከድህነት ለመውጣት የሚደረገው ርብርብ ይቀጥላልም ብለዋል።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ሀይሉ ጀልዴ በበኩላቸው የነዋሪውን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
''በከተማዋ የተቀመጠውን የልማት ግብ ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል'' ያሉት ከንቲባው በከተማዋ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።
በተመሳሳይም በከተማዋ የአገልግሎት አሰጣጥን በዲጂታል ዘዴ በመደገፍ በአብዛኛው ዘርፍ መስሪያ ቤቶች ከወረቀት ነፃ የሆነ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በዚህም 122 አገልግሎቶች ወደ ዲጂታል እንዲገቡ ከማድረግ ባለፈ ከ30 በላይ የዘርፍ መስሪያ ቤቶች የአንድ ማዕከል አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም አክለዋል።
ዛሬ የተመረቁ ፕሮጀክቶችም በህዝብ ተሳትፎ፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎትና በየደረጃው ባለው የአስተዳድሩ መዋቅር ጥረት የተገነቡ መሆናቸውን አውስተዋል።
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025