
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ሙስናን በተመለከተ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን ብለዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስታዊ ሙስና የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገር ግን ከአገልግሎት አንጻር ትናንሽ የሙስና ተግባራት አሉ ብለዋል።
ይህን ለማስተካከል ወደ ስራ የገባው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሶስት ወራት ብቻ 23 ተቋማትን በማካተት 124 አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
አሁን አንድ ማዕከል ብቻ ነው ያለው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እስከ መስከረም ድረስ 17 እናደርሳለን መሶብ እየተስፋፋ አገልግሎት እየዘመነ ሲሄድ የእጅ በእጅ ሙስና እየቀነሰ ይሄዳል ሲሉም አስታውቀዋል።
ከዚያ ውጭ ሙስናን መፀየፍ የግለሰቦችን አመለካከትና ውሳኔን የሚጠይቅ መሆኑንም ማወቅ ይገባል ነው ያሉት።
ሙስናን የምንከላከለው በስርዓት ነው፤ በዘረጋነው የመሶብ ስርዓትም ተገልጋዮች ከ90 በመቶ በላይ እርካታ አሳይተዋል ይህንን በሁሉም አካባቢዎች ማስፋት ከተቻለ ሙስና በእጅጉ ይቀንሳል ብለዋል በማብራሪያቸው።
ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...
Apr 14, 2026
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025