የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ምንም አይነት የነዳጅ የዋጋ ጭማሪም ሆነ የአቅርቦት እጥረት የለም - የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር

Jun 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ ምንም አይነት የነዳጅ የዋጋ ጭማሪም ሆነ የአቅርቦት እጥረት አለመኖሩን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።

ከትላንት ጀምሮ በአዲስ አበባ ምንም አይነት የነዳጅ አቅርቦት እጥረት አለመኖሩን አስመልክቶ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም በቂ ነዳጅ በየጊዜው እየገባ መሆኑን ነው የተናገሩት።

ነገር ግን በስግብግብ ነጋዴዎች ምክንያት የነዳጅ እጥረት እንዳለ ለማስመሰል ሙከራ መደረጉን ገልጸዋል።

ይህን ባደረጉ ሁለት የነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ጠቁመው፤ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.