
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ ምንም አይነት የነዳጅ የዋጋ ጭማሪም ሆነ የአቅርቦት እጥረት አለመኖሩን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።
ከትላንት ጀምሮ በአዲስ አበባ ምንም አይነት የነዳጅ አቅርቦት እጥረት አለመኖሩን አስመልክቶ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በቂ ነዳጅ በየጊዜው እየገባ መሆኑን ነው የተናገሩት።
ነገር ግን በስግብግብ ነጋዴዎች ምክንያት የነዳጅ እጥረት እንዳለ ለማስመሰል ሙከራ መደረጉን ገልጸዋል።
ይህን ባደረጉ ሁለት የነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን ጠቁመው፤ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025