
ጅማ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ በተለያዩ ሐይቆች ላይ በዘመናዊ ጀልባዎች የታገዘ የውኃ ላይ ትራንስፖርት ለመስጠት ጥረት እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ገለጸ።
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ(ዶ/ር) እንዳሉት ዘመናዊ እና ቀልጣፋ የሀገር ውስጥ የውኃ ትራንስፖርት እንዲኖር እየተሰራ ነው።
ለዚህም የሚያግዙ ዘመናዊ ጀልባዎችን በማስመጣት በሀገር ውስጥ ሐይቆች ላይ ትራንስፖርትን ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ 'ጣና ነሽ 2' ለዚሁ አገልግሎት ወደ መዳረሻዋ ባህር ዳር እየተጓጓዘች መሆኑን ተናግረዋል።
ጀልባዋ 188 ሰዎችን የመጫን አቅም እንዳላትና ይህም ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ ያስችላል ብለዋል።
በቀጣይም እንደ 'ጣና ነሽ 2' አይነት ዘመናዊ ጀልባዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የሀገር ውስጥ የውኃ ትራንስፖርትን በማሻሻል የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ የሚያገኘውን ገቢ ለማሳደግ ይሰራል ብለዋል።
ላንጋኖ እና ሻላን ጨምሮ በሁሉም ሐይቆች ላይ በዘመናዊ ጀልባዎች የታገዘ የውኃ ላይ ትራንስፖርት ለመስጠት እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
አያይዘውም የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ በዓለም ላይ የመዳረሻ ወደቦችን ብዛት ወደ 350 ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የጭነት አቅምም ከፍ እንዲል ይደረጋል ብለዋል።
ከገቢ አንጻርም በዘጠኝ ወር አፈጻጸም የተሻለ ገቢ መገኘቱን ገልጸው፣ ይህንንም አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ተቋሙን ከማንዋል አሰራር በማላቀቅ የዲጂታላይዜሽን አሰራር እየተተገበረ መሆኑን ገልጸው ይህም ወጪን ከመቆጠብና ገቢን ከመጨመር ባለፈ ግልጽ አሰራር ለመዘርጋት ያስቻለ መሆኑን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ በጅማ ከተማ ለአቅመ ደካሞች ያደሰውን መኖሪያ ቤት ለነዋሪዎች ማስረከቡ ይታወቃል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025