
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 23/2017(ኢዜአ)፦መንግስት በኢንቨስትመንት ዘርፍ ተግባራዊ እያደረገ ያለው ሪፎርም ምቹ የኢንቨስትመንትና ቢዝነስ ከባቢ እየፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ገለፁ።
የኦሮሚያ ክልል የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴና አማራጮች ዙሪያ ፎረም ተካሂዷል።

በፎረሙ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ አሕመድ እድሪስ እና ባለሃብቶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት እንደ ሀገር ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት በርካታ የሪፎርም ተግባራት መከናወኑን ተናግረዋል።
የህግን ጨምሮ የፖሊሲ፣ የአሰራር እና ሌሎች አስፈላጊ ማሻሻያዎች መደረጋቸውን አንስተዋል።
ማሻሻያዎቹ ተገማች የሆነ የኢንቨስትመንት እና የቢዝነስ ከባቢን ለመጥፈር እያስቻሉ መሆናቸውንም ገልጸው፤ ባለሃብቶች በምቹ ሁኔታ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የሚያስችል መሆኑንም አስታውቀዋል።
ባለሃብቶች ይህን እድል በመጠቀም ኢንቨስት እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ በበኩላቸው ከለውጡ ወዲህ እንደ ሀገር የተወሰዱ የኢንቨስትመንት ማሻሻያዎች የኢንዱስትሪ ዘርፉን በከፍተኛ መጠን ማነቃቃቱን አንስተዋል።
በተለይ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪውን ምርታማ እንዲሆን፣ የዘርፉ ማነቆዎች እንዲፈቱ እና ለተጨማሪ ኢንቨስትመንቶች ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም አስታውቀዋል፡
ይህንን ተከትሎ በኢንዱስትሪ ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑንም ተናግረዋል።
መንግስት ኢንዱስትሪዎች የሚያጋጥማቸውን ችግር ለመፍታት የአምራች ኢንዱስትሪ ምክርቤት በማቋቋም እየሰራ እንደሚገኝም ጨምረው ገልጸዋል።

የኦሮሚያ መሬት ቢሮ ኃላፊ መሰረት አሰፋ እንዳሉት ቢሮው ከኢንቨስትመንት ቢሮ ጋር በቅንጅት ኢንቨስተሮች በክልሉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ አስራር ተዘርግቷል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025